@user2565750246217:

user2565750246217
user2565750246217
Open In TikTok:
Region: MX
Saturday 31 January 2026 17:50:33 GMT
195
21
1
1

Music

Download

Comments

almaruiz1972
Alma :
igualito 😂😂😏
2026-02-01 00:31:17
0
To see more videos from user @user2565750246217, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

#creatorsearchinsights  🟢🟡🔴 ኅዳር 28 | ከ9ኙ ቅዱሳን አንዱ #አቡነ_ሊቃኖስ ተሰወሩ። እኚህ ቅዱስ እንደ 8ቱ ጓደኞቻቸው ከነገሥታት ቤተሰብ የተገኙ እና ምንኩስናን መርጠው ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ናቸው።
#creatorsearchinsights 🟢🟡🔴 ኅዳር 28 | ከ9ኙ ቅዱሳን አንዱ #አቡነ_ሊቃኖስ ተሰወሩ። እኚህ ቅዱስ እንደ 8ቱ ጓደኞቻቸው ከነገሥታት ቤተሰብ የተገኙ እና ምንኩስናን መርጠው ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ናቸው። "አባ ሊቃኖስ" የመጀመሪያ ስማቸው ሳይሆን በእውቀታቸው የተደመመ የአክሱም ሕዝብ ያወጣላቸው ስም ነው። ሊቃኖስን 'ሊቁ አባት' ማለት ነው ብለው የተረጎሙልን አበው አሉና። አቡነ ሊቃኖስ ከዘጠኙ ቅዱሳን ውስጥ አቡነ ሊቃኖስ ለየት የሚሉበት ነገር ቢኖር ዓሥሩም የእጆቻቸውና የእግሮቻቸው ጣቶች እንደፋና ያበሩ ነበር፡፡ ሁልጊዜም ለአገልግሎት ሲወጡ በትረ ሙሴአቸውን አይለዩም ነበር። ሲሰብኩም፣ ሲጸልዩም ተደግፈውባት ነበር። ታዲያ ከዘመን ብዛት የሚደገፉባት የእጃቸው መዳፍ መነደሉን አበው፦ "ወበእሒዘ በትር ዘተሰቁረ ዕዱ" ሲሉ ይናገራሉ። የአቡነ ሊቃኖስ ገዳማቸው በደብረ ቁናጽል (የቀበሮዎች ተራራ) አክሱም ከጓደኛቸው ከአባ ጰንጠሌዎን ገዳም አቅራቢያ ይገኛል፡፡ ጻድቁ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደረጉ ነበር፡፡ መላእክትም ዘወትር ባለመለየት ይጎበኙዋቸው ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዘወትር እየተገለጠላቸው ይባርካቸውና ቃልኪዳን ይሰጣቸው ነበር፡፡ በገዳማቸውም ልክ በደብረ ታቦር እንደተገለጠ በግርማው ታይቷቸዋል። በጸሎታቸውም አጋንንትን አውጥተዋል፣ ድውያንን ፈውሰዋል፣ ዕውራንን አብርተዋል፣ ሙታንን አንሥተዋል፡፡ ከተስዓቱ ቅዱሳን ውስጥ አራቱ ሞትን ሳያዩ ተሰውረዋል፡፡ አቡነ አረጋዊ ጥቅምት 14 ቀን ተሰወሩ፡፡ አቡነ ገሪማ ሰኔ 17 ቀን፣ አቡነ አፍጼ ግንቦት 29 ቀን፣ አቡነ ሊቃኖስ ኅዳር 28 ቀን ተሰወሩ፡፡ ◦🍀◦ በአርያኖስ እጅ ሰማዕት የሆኑት ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_ሰረባሞን በዓላቸው ነው።

About