@tecnocelltoo: 🎧 Fone Sem Fio Kaidi KD-780 – Branco 🔹 Áudio limpo e potente 🔹 Conexão Bluetooth estável 🔹 Bateria de longa duração 🔹 Design moderno e confortável Garanta já o seu! 📲🤍

tecnocell
tecnocell
Open In TikTok:
Region: BR
Thursday 12 February 2026 19:28:58 GMT
810
18
0
25

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @tecnocelltoo, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

☑️አንዲት የስንዴ ቅንጣት ሰላሳ ስልሳ መቶ ፍሬ ለማፍራት ከጎተራ ወጥታ  ወደ መሬት ትወድቃለች፣ከአፈር ጋር ትደባለቃለች፣ትበሰብሳለች ከዚያ በኋላ  ታድሳ ቡቃያ ሁና መቃብር ፈንቅላ ትወጣለች። ☑️ከዚህ ቀጥሎ  እጅግ ማራኪ ታይቶ የማይጠገብ መልክ፣ውበት፣ጌጥ ያላት ትሆናለች።ቅጠሏ፣አበባዋ፣ፍሬዋ፣እሸቷና መዓዛዋ ሁሉ ነገሯ የሚያስጎመጅ ይሆናል። ከዚህ ለመድረስ የከፈለችው ዋጋ  እስከሞት ድረስ ነው።የሰው ሕይወት እንዲሁ ነው  ያልተፈተነ ሕይወት ገለባ ነው።ከገለባ ምንም አይጠበቅም።በፈተና ካልተሰራና ካልተስተካከለ ሕይወት የጽድቅን ፍሬ መጠበቅ እራስን ማታለል ነው። ☑️እንኳን ለመጽደቅ በረከት ለማግኘት ሥጋዊው ኑሮ የተሳካ እንዲሆን የምንከፍለው ዋጋ ቀላል አይደለም።በተለያየ ዓለም ተሰደን፣ተበትነን ከቤተሰብ ተለይተን፣ክፉና በጎ እየሰማን፣የቤተሰብ የሀገር ናፍቆት ሁሉ ችለን የምንኖረው ኑሯችን የተሻለ እንዲሆን ነው።ይህን አላደርግም ያለ ከነችግሩ ይኖራል። ☑️አንድ ሰው ቤተሰብ አፍርቶ፣ልጅ ወልዶ፣በዘመድ ከብሮ፣ ድሮ፣ኩሎ፣ሹሞ ተሸልሞ  ለመኖር  እራሱን ለፈተና ማዘጋጀት አለበት።ያ ካልሆነ ለዚህ ክብር አይበቃም። ፈተናን ታግሰህ ካላለፍክ ፍሬውን ታይዋለህ እንጂ አትበላውም።ዋጋ ያልከፈለ ሰው እንደተባለው እንደተመኘው ይቀራል እንጂ መቼም ሊያገኘው አይችልም።መንፈሳዊው ሕይወት ደግሞ  ከዚህ በላይ ዋጋ ያስከፍላል። ☑️ሥጋዊው ቤት ጊዜያዊ ነው።መንፈሳዊው ቤት ዘላለማዊ ስለሆነ ከዚህ በላይ በእጥፍ ትዕግሥት ይጠይቃል።ጠላትን መውደድ፣በሥጋው በደሙ ተወስኖ መኖር፣ትዕዛዛቱን መጠበቅ፣ከቂም ከበቀል መጽዳት፣በንስሐ መኖር፣መከራ መስቀሉን መሸከም፣መጾም መጸለይ፣ንፁህ ልብና እውነተኛ ፍቅርን ይጠይቃል። ☑️በዚህ ያልተፈተነ ሕይወት የጽድቅ ፍሬ ማፍራት አይችልም።ቅዱሳን ሐዋርያት “በመፈተናችን ደስ ይለናል” ያሉት መፈተናቸው የፍሬያቸው ምልክት ስለሆነ ነው።የገለባ ሳይሆን የዘር ሕይወት ይኑረን።በቅጠል እንዳንቀር ለፍሬ እንድንበቃ መንፈስ ቅዱስ ያግዘን  ፈተናችንን ሁሉ ለበረከት ያድርግልን አሜን።እምነት ይኑረን ተስፋን አንጣ በፈተና እንፅና‼️ 🕊️ሁሉም ይማርበት ዘንድ ሸር አድርጉት🫴🏾 እግዚአብሔር ማስተዋልን ጥበብን እውቀትን ከፍቅር ጋር ይስጠን አሜን🙏እግዚአብሔር ብርሃኔና-መድሃኒቴ ነው።
☑️አንዲት የስንዴ ቅንጣት ሰላሳ ስልሳ መቶ ፍሬ ለማፍራት ከጎተራ ወጥታ ወደ መሬት ትወድቃለች፣ከአፈር ጋር ትደባለቃለች፣ትበሰብሳለች ከዚያ በኋላ ታድሳ ቡቃያ ሁና መቃብር ፈንቅላ ትወጣለች። ☑️ከዚህ ቀጥሎ እጅግ ማራኪ ታይቶ የማይጠገብ መልክ፣ውበት፣ጌጥ ያላት ትሆናለች።ቅጠሏ፣አበባዋ፣ፍሬዋ፣እሸቷና መዓዛዋ ሁሉ ነገሯ የሚያስጎመጅ ይሆናል። ከዚህ ለመድረስ የከፈለችው ዋጋ እስከሞት ድረስ ነው።የሰው ሕይወት እንዲሁ ነው ያልተፈተነ ሕይወት ገለባ ነው።ከገለባ ምንም አይጠበቅም።በፈተና ካልተሰራና ካልተስተካከለ ሕይወት የጽድቅን ፍሬ መጠበቅ እራስን ማታለል ነው። ☑️እንኳን ለመጽደቅ በረከት ለማግኘት ሥጋዊው ኑሮ የተሳካ እንዲሆን የምንከፍለው ዋጋ ቀላል አይደለም።በተለያየ ዓለም ተሰደን፣ተበትነን ከቤተሰብ ተለይተን፣ክፉና በጎ እየሰማን፣የቤተሰብ የሀገር ናፍቆት ሁሉ ችለን የምንኖረው ኑሯችን የተሻለ እንዲሆን ነው።ይህን አላደርግም ያለ ከነችግሩ ይኖራል። ☑️አንድ ሰው ቤተሰብ አፍርቶ፣ልጅ ወልዶ፣በዘመድ ከብሮ፣ ድሮ፣ኩሎ፣ሹሞ ተሸልሞ ለመኖር እራሱን ለፈተና ማዘጋጀት አለበት።ያ ካልሆነ ለዚህ ክብር አይበቃም። ፈተናን ታግሰህ ካላለፍክ ፍሬውን ታይዋለህ እንጂ አትበላውም።ዋጋ ያልከፈለ ሰው እንደተባለው እንደተመኘው ይቀራል እንጂ መቼም ሊያገኘው አይችልም።መንፈሳዊው ሕይወት ደግሞ ከዚህ በላይ ዋጋ ያስከፍላል። ☑️ሥጋዊው ቤት ጊዜያዊ ነው።መንፈሳዊው ቤት ዘላለማዊ ስለሆነ ከዚህ በላይ በእጥፍ ትዕግሥት ይጠይቃል።ጠላትን መውደድ፣በሥጋው በደሙ ተወስኖ መኖር፣ትዕዛዛቱን መጠበቅ፣ከቂም ከበቀል መጽዳት፣በንስሐ መኖር፣መከራ መስቀሉን መሸከም፣መጾም መጸለይ፣ንፁህ ልብና እውነተኛ ፍቅርን ይጠይቃል። ☑️በዚህ ያልተፈተነ ሕይወት የጽድቅ ፍሬ ማፍራት አይችልም።ቅዱሳን ሐዋርያት “በመፈተናችን ደስ ይለናል” ያሉት መፈተናቸው የፍሬያቸው ምልክት ስለሆነ ነው።የገለባ ሳይሆን የዘር ሕይወት ይኑረን።በቅጠል እንዳንቀር ለፍሬ እንድንበቃ መንፈስ ቅዱስ ያግዘን ፈተናችንን ሁሉ ለበረከት ያድርግልን አሜን።እምነት ይኑረን ተስፋን አንጣ በፈተና እንፅና‼️ 🕊️ሁሉም ይማርበት ዘንድ ሸር አድርጉት🫴🏾 እግዚአብሔር ማስተዋልን ጥበብን እውቀትን ከፍቅር ጋር ይስጠን አሜን🙏እግዚአብሔር ብርሃኔና-መድሃኒቴ ነው።

About