@biruk.marshet: ዓርብ፦ ቤተክርስቲያን ይባላል። "…ትንቢት የተነገረለት፣ ሱባኤ የተቆጠረለት የጌታችን ከልደቱ እስከ ሞቱ ያደረገው የማዳን ጉዞ በመስቀል ላይ የተፈጸመበት፣ ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ተገርፎ፣ የእሾኽ አክሊል ደፍቶ፣ እጅና እግሩን በችንካር፣ ጎኑን በጦር ተወግቶ ደሙ እንደ ጎርፍ አፈስሶ የመዳናችን ዐዋጅ የታወጀበት ዕለት ነው። "…ጌታ በመስቀል ላይ ሳለ የከበረ ደሙን ዑራኤል መልአክ በወርቅ ፅዋ ቀድቶ በዓለሙ ሁሉ ረጭቶታል። የጌታ ደም በነጠበበት ቦታ ሁሉ እግዚአብሔር ባወቀ ቤተክርስቲያንን ሠርቷቷል። ከጌታ ሞትና ትንሣኤም በኋላ ቢሆን ዛሬ ድረስ አዲስ ቤተክርስቲያን የሚታነጸው ደመ ክርስቶስ ከነጠበበት ስፍራ ነው። ቤተክርስቲያን የወልደ እግዚአብሔርን ፍጹም ሰው መሆንና ፍጹም አምላክ መሆን አምነን፣ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ተወልደን በስመ ሥላሴ ተጠምቀን ሐብተ ወልድና ስመ ክርስትና አግኝተን፣ በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ ውሉድ ተብለን ተጠርተን የምንኖርባት የአምላካችን ቤት ናት። "…ቤተ ክርስቲያን ድንገት የተመሠረተች አይደለችም። ቅድመ ዓለም በአምላክ ልቡና ታስባ፣ በዓለመ መላእክት ተወጥና በአማን ጐልታ፣ ግዘፍም ነሥታ የተመሠረተችው ግን በዕለተ አርብ በደመ ክርስቶስ ተቀድሳ፣ በትንሣኤው ከብራ፣ ንጽሕትና ጽሪት ባደረጋት ጊዜ ነው። ክርስቶስ ሞቶ ባይነሣ ኖሮ ግን ቤተክርስቲያን ሕልውና አይኖራትም ነበር። "…ከአዳም መውደቅ በኋላ ለ5,500 ዓመታት በሲዖል ተግዘው የነበሩ ነፍሳት ከዓመተ ፍዳ ዓመተ ኩነኔ የጌታ ደም ፈሶላቸው የትንሣኤው ብርሃን ደርሷቸው ከዲያብሎስ አገዛዝ ነጻ የወጡበትና ገነት የገቡበት ቀንም ስለሆነ ዕለቱ እንዲህም ተዘክሮ ይዋላል። ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍሥሐ ወሰላም።
ብሩክ ማርሸት-BIRUK MARSHET
Region: ET
Friday 17 April 2026 07:57:42 GMT
Music
Download
Comments
ጋሻው :
አሜን አሜን አሜን
2026-06-20 11:44:40
0
ሰው መሆን ይቀድማል💟🙏💟 :
Amen 🙏 🙏 🙏
2026-04-18 03:56:58
1
emebet :
አሜን🙏🙏🙏
2026-07-07 08:15:16
0
Mebrat meki :
አሜን አሜን አሜን 🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰
2026-06-01 10:08:47
0
ሚሊዮን☦️ :
አሜን
2026-05-16 20:09:59
0
ማርያም እናቴ :
አሜን አሜን አሜን 🙏🙏🙏
2026-04-17 12:26:25
0
abushe ficha :
🥰🥰🥰
2026-05-15 17:48:24
0
እግዚአብሔር ሆይ መንገደን አሳየኝ :
🥰🥰🥰🥰🥰
2026-05-07 08:52:33
0
muluneh :
🥰🥰🥰
2026-04-17 19:33:48
0
adu love :
❤️❤️❤️
2026-05-18 15:43:39
0
To see more videos from user @biruk.marshet, please go to the Tikwm
homepage.