@calerhome: Wing chair design exclusive #calerhome #fyp #foryou

CALER HOME FURNITURE
CALER HOME FURNITURE
Open In TikTok:
Region: MY
Sunday 24 May 2026 04:04:43 GMT
7258
12
0
35

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @calerhome, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

#አርሲ #arsi እሁድ መስቀል አደባባይ የኦርቶዶክስ ሰላማዊ ሰልፍ አይቀርም ➻የሞ*ት ዜና መዘገቡ ሰልችቶናል፦ይቺም ሻማ ሰልችታለች! =
#አርሲ #arsi እሁድ መስቀል አደባባይ የኦርቶዶክስ ሰላማዊ ሰልፍ አይቀርም ➻የሞ*ት ዜና መዘገቡ ሰልችቶናል፦ይቺም ሻማ ሰልችታለች! ="የምስራቅ አርሲ ወገኖችህ በችግር ውስጥ ሆነው በገጽህ ድምፅ የማትሆን ኢትዮጵያዊ፣ ነገ ሕሊናህ መታዘቡ አይቀርም። ይህንን እወቅ፤🚨 "እባካችሁ ድምፅ ሁኑን!" — ከምስራቅ አርሲ ጫካዎች የተሰማ የድረሱልን ጥሪ! መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል። 📌 እስካሁን የደረሰው ጉዳት፦ የሕይወት መጥፋት፦ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል። የንብረት ውድመት፦234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል። የሃይማኖት ተቋማት፦ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል። ⚠️ ወቅታዊ ሁኔታ፦ ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ። 🙏 ነፍስ ይማር! ምንም ለማድረግ አቅሙ ባይኖርህ እንኳ ቢያንስ አጋርነትህንና አዘኔታህን መግለጽ ትልቅ ነገር ነው።"😭============== በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃላይ ሳናይ የምንሞተው ነገር የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ''ኃላፊነቴን በአግባቡ ስላልተወጣሁ ሥራዬን በፈቃዴ ለቅቄያለሁ፤ ከ'ኔ የተሻለ ሰው ይምራው'' የሚለው ነው። በአርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና አማኞች እና አብያተ-ክርስትያናት ላይ በተደጋጋሚ ጥቃቶች እየተሰነዘሩ ብዙ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ሞተ፤ አብያተ-ክርስትያናት እና ቅርሶችም ወደሙ፤ በነዋሪዎቹ ዘንድ ሥጋትና ጥርጣሬ ሰፈነ። ይሄን ተደጋጋሚ ጥቃት ለማስቀረት የተሠራ ሥራ አለ? ሰላም ማስከበር 100% የክልሉ መንግሥት ሥራ አይደለም እንዴ? ምን አድርጓል? ሰላም ማስከበር ካቃታቸው በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ''አልቻልንም፤ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ ይግባልን'' ይባላል እኮ! መቼም ''እኔ ለዚህ ኃላፊነት ብቁ ሆኜ አልተገኘሁም፤ የተሻለ ብስለትና ልምድ ያለው ሰው ይተካኝ'' የሚሉ ኃላፊዎችን በሕይወት እያለን እንደማናይ ዕሙን ነው። ሰው ባለቀ ቁጥር ይቺን ሻማ ብልጭ ማድረግ ምን ፋይዳ አለው? ይሰለቻል። የክልሉ መንግሥት ለዚህ ዞን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሕዝቡን ይጠብቅ። በጊዜ መፍትሔ ካልተሰጠው የዚህ ዳፋ የማይተርፈው ሰው የለም። እንደ አንድ ተርታ ዜጋ በደረሰው ጉዳት ሐዘኔን ለመግለጽ እወዳለሁ። 😥 Awlet Ahmed ◈የተቃጠለ እና የተዘጋ ቤተመቅደስ፣ያለቀ እና የተሳደደ ክርስቲያን፣ የወደመ እና የተሰረቀ ቅርስ፣ ያለቀ ንብረት እየቆጠርን የምንኖረው እስከመቸ ነው? ◈በየደብሩ ያላችሁ መምህራን ◈በየመዋቅሩ ያላችው ተቆርቋሪ አባቶች ◈በየሰንበት ትቤቱ እና በማኅበራት ውስጥ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን ◈ከዚህ በላይ ምን ዓይነት የጥፋት ምልክት ማየት ትፈልጋላችሁ? ➻መ*ሞት እኮ ትልቅ ዕረፍት ነው። ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መቀበል ያለብንን ሁሉ ተቀብለን ብንሞት ትልቅ ጸጋ ነው። ◈ከዚህ በላይ ውድመቱ ከቀጠለ ነበሩ በሚለው ትርክት ይቋጫል። ደግሞም በአርሲና በገጠሩ ኦሮምያ ቁመን እየሄድን ዐይናችን እያየ ነበሩ በሚለው ታሪክ እየተቋጨ ነው። ◈ክርስቲያኑ ማኅበረ ሰብ የሚበዛበትን ክፍል፡ ተረክ ፈጥሮ፡ ሰሜኑን ለጦርነት ብሎ ፈርጆ፦ በጦር እና በረሀብ፣ በማፈናቀልና በስደት፣ አሳሩን ሲያበላው ከባጀ አምስተኛ ዓመቱ ነው። ◈የብልጽግና ሥርዓት ብትወደው እንኳ ኦርቶዶክስ በመሆንህ አዛኘን ነው የምልህ አይለቅህም። ጊዜ ጠብቆ ነጣጥሎ ያጠፋሀል። ◈ጠላቱ ኦርቶዶክስነት እና አጠቃላይ በእስልምናም ነባርነት ያለው ባለእሴቱ ሕዝብ ነው። ◈እኔ በግሌ ከዚህ ድክርት የሞ*ት ሥርዓት ለሃይማኖታችን እና ለሀገራችንን የሚጠቅም አንዲትም መልካም ነጥብ አላገኘሁበትም። ◈በያለንበት በውስጥም በውጪም እንተባበርና ቤተ ክርስቲያናችንንም ሀገራችንንም ከጥፋት እንታደግ!! ➻የሞ*ት ዜና መዘገብ ሰልችቶናል። መምህር ገብረ መድኅን እንየው ግንቦት 25/2018 ዓ.ምስለ አርሲ ኦርቶዶክሳዊያን ጅምላ ጭፍጨፋ ዝም አንልም ፍትህ ለአርሲ ባለማተብ ኦርቶዶክሶች እያላችሁ ፃፏ STOP GENOICEDE CRISTANS IN አትሆፕአ #ethiopian_tik_tok🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ፀንታ_ለዘለዓለም_ትኑር #news

About