@luanaiindica: Guarda-chuva automático com abertura e fechamento em um único botão, perfeito para o inverno, dias de chuva e vento forte ☔ Possui hastes duplas super resistentes, design moderno e alça ergonômica com gancho, ideal para prender na bolsa ou mochila. Além da chuva, também tem proteção solar, sendo ótimo para o dia a dia, trabalho, escola ou viagens. #guardachuvaautomático #guardachuva #guardachuvareforçado

Luana Araújo
Luana Araújo
Open In TikTok:
Region: BR
Friday 19 June 2026 22:53:05 GMT
165
1
0
0

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @luanaiindica, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

'ቀዘብዬ'🌹🥹 ✨ውድ ቤተሰቦቼ ለመሆኑ ቴዲ አፍሮ በመቀሌ ህዝብ ከመወደዱ የተነሳ የኮንሰርት ቀን እንዲጨምር ተጠይቆ እንደነበር ታውቃላቹ?🤔 ዛሬ ለየት ባለ መልኩ ይሄንን በዳዊት መለሰ አበረታችነት ቴዲ አፍሮ ለሌሎች ሙዚቀኞች አዘጋጅቶት የነበሩትን ግጥም እና ዜማዎች አቧራቸውን አራግፎ ወደ ሙዚቃው ዘው ብሎ የገባበትትን ቀድሞ ቢሰራም በሁለተኛ አልበምነት ቴዎድሮስ ካሳሁን ብሎ በ94 ካሳተመው አልበም ላይ 'ቀዘብዬ'ን ጋብዣቹ የመቀሌው የ1994 ኮንሰርትና ባለሙያዎቹ ሲዘከሩ እንዲህ ነበር፡-  ብለን አንድ የታሪክ ኩነት መዘን እናስታውሳለን🥰  ✍️ቴዲ 'አቦጊዳ' አልበሙን በ1993 መገባደጃ ላይ ይዞ ብቅ ሲል ቴዲ አፍሮ ማን ነው? የሚል ጥያቄ ጎረፈ፡፡ እድሜ ለኤፍኤም አዲስ 97.1 ዲጄዎችና የኪነጥበብ ፕሮግራም አዘጋጆች፡፡ እነ ዲጄ ዚ፣ አዲስ ዜማዎች፣ አይሬ፣ ዲጄ ኪን፣ አፍሪካ ጃዝ መንደርና ሌሎችም ደጋግመው ለህዝብ ስላስደመጡት ቴዲ በደንብ ከህዝብ ጋር መተዋወቅ ጀመረ፡፡ በዝነኛው የአለቤ ሾው ፕሮግራም ላይ ሲቀርብ ደግሞ ስሙ ናኘ፡፡ የቴዲ ተቀባይነት በጥቂት ወራቶች ከማንም በላይ ገዘፈ፡፡  በዚህ ጊዜ ነበር ከአቦጊዳ አልበም በፊት የሰራውና ለሙዚቃ አሳታሚ የሸጠው ጽጌረዳ/ቀዘብዬ የተባለው አልበሙ ሁለተኛ አልበም ተብሎ የተለቀቀው፡፡ በጊዜው ቴዲ አፍሮ የስራውን መለቀቅ ቢቃወምም ቀድሞ የሸጠው በመሆኑ ሙዚቃ አሳታሚው አልበሙን የማሰራጨት ሙሉ መብት ስለነበረው አለመግባባቱ በዛው ነበር የተቋጨው፡፡ ጽጌረዳ እንደ አቦጊዳ ባይሆንም ቴዲ አፍሮ ተደማጭነትና ዝናን አላጣም፡፡ በጽጌረዳ አልበም ውዝግብ ብቻ ሳይሆን የሴት ልጅ ጡት ላይ ፈረመ የሚሉ የማጥላላት ዘመቻዎች በሰፊው ተከፈተበት፡፡ ነገር ግን የያኔው የእሁድ ከሰአት የ 120 ቲቪ ፕሮግራም ላይ ቀርቦ አጥጋቢ መልስ በመስጠቱ ሁሉም በዛው ተደመደመ፡፡ ከነዚህ አልበሞች ተከታትሎ መለቀቅ በኋላ ቴዲ በአዲስ አበባና በየክልሉ እየዞረ ኮንሰርት ማቅረቡን ቀጠለ፡፡ የተለያዩ ፕሮሞተሮችና ፕሮዲዩሰሮች አይናቸውን ጣሉበት፡፡ በዚህ ወቅት ደግሞ ከዝነኛው የሙዚቃ አቀናባሪና የያኔው የኮንሰርት ፕሮሞተር አማኑኤል ይልማ ጋር ተገናኘ፡፡  ወጣቱ አቀናባሪና ፕሮሞተር አማኑኤል ይልማ መቀሌ ከተማ ላይ ደጋግሞ ኮንሰርቶችን ያሰራ ነበር፡፡ ዝነኛው የመቀሌ ከተማ ባህላዊ ባርና ሬስቶራንት ገዛ ገርላሳ ደግሞ ቤቱ ነበር፡፡ እዚህ ፈረንጅ የሚጎርፍበት ቤት ፍቅራዲስ ነቃጥበብን ሁለት ጊዜ የወሰደ ሲሆን ፍቅራዲስ አክሱም ጭምር ተሻግራ በተመሳሳይ ሰርታለች፡፡ ከአማኑኤል ጋር በመሆን ገዛ ገርላሳ ላይ እንደ ህብስት ጥሩነህ፣ ይርዳው ጤናው፣ ደረጀና ሀብቴ የመሳሰሉ አርቲስቶች ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በ 1994 ጥር 24 እና 25 ኮንሰርት ለማቅረብ ቀጠሮ የተያዘለት ባለተረኛ ደግሞ የጊዜው ባለዝነኛ ቴዲ አፍሮ ነበር፡፡  ይህን ኮንሰርት ለማቅረብ ለቴዲ አፍሮ 40 ሺህ ብር ሊከፈለው ተስማምቶ ለሁለት ቀናት ከአነ አማኑኤል ጋር ወደመቀሌ አቀኑ፡፡ የመቀሌ ህዝብ ቴዲ ባቀረበው ኮንሰርት እጅግ ተደሰተ፡፡ ነገር ግን ገዛ ገርላሳ በሁለት ቀናት ውስጥ ለመቀሌ ህዝብ ቴዲን ለማሳየት በቂ አልነበረም፡፡ በቦታ ጥበት ብዙዎች ኮንሰርቱ አመለጣቸው፡፡ በዚህ የተነሳ ቴዲ አንድ ቀን አድሮ ኮንሰርቱን እንዲሰራ ለእነ አማኑኤል የህዝብ ጥያቄ ጎረፈ፡፡ የመቀሌ ህዝብ ፍቅር ያሸነፈው ቴዲ ለጥያቄው አላመነታም፡፡ ለአንድ ተጨማሪ ቀን ኮንሰርቱን ለማራዘም ቴዲና አዘጋጆቹ ተስማሙ፡፡ ዝግጅቱ የተሳካና የተዋጣለት ሆኖ በዚሁ ተጠናቀቀ፡፡  ቴዲ አፍሮ በመቀሌ ቆይታው ለመቀሌ አድናቂዎቹ ያለውን በሙሉ ለመስጠትና ለማስደሰት ሞክሯል፡፡ ከሁለቱ አልበሞቹ ዘፈኖች በተጨማሪም አለምብሬ የተባለውን የጉራጊኛ ዘፈን ያቀረበ ሲሆን ኦሮሚኛ ዘፈን ጭምር ለህዝቡ ተጫውቷል፡፡ በትግርኛም መድረኩን አድምቋል፡፡ ደማቁ የዛን ጊዜው መድረክ ቴዲ አፍሮ ለሚወደው የመቀሌ ሙዚቃ አፍቃሪ ብዙ ደስታን የሰጠበትና ብዙ ፍቅር የሸመተበት ነበር፡፡ ይህ ከሆነ ከሶስት አመት በኀላ ቴዲ አፍሮ በያስተሰርያል አልበሙ ወደህዝብ ጆሮ ብቅ አለ፡፡ ስለሀገር ፍቅርና አንድነት በዘፈኖቹ የሰበከው ከያኒ ውለታው ተረስቶ ውግዝ ከማእርዮስ ተባለ፡፡ እየሩሳሌም ብሎ ለቅድስቲቱ ሀገር ሰላም ጮኸ፡ ቀነኒ ኬኛ ብሎ በአትሌቶቻችን የኦሎምፒክ ገድል የሀገር ፍቅር ቀሰቀሰ፡ ብዙዎችን በስሜት እምባ አራጨ፡ ቴዲ አፍሮ ወደሙዚቃው ከተቀላቀለ በኀላ ብዙ ባለተሰጥኦ ወጣቶች ፈለጉን ተከትለው መብቀል ጀመሩ፡፡  ይህ ሁሉ ግን 97 ላይ በዘፈነው ያስተሰርያል ተረሳ፡፡ መንግስት ዘፈኑ በማንኛውም ጣቢያ እንዳይደመጥ እቀባ ጣለ፡፡ ኢህአዴግ ልክ በግል እንደሚያሳድደው ደመኛው እግር በእግር እየተከታተለ ኮንሰርቱን ሰረዘበት፡፡ ቴዲ በሀገሩ ባይተዋር ተደረገ፡፡ ፍቅር የዘፈነባቸው መቀሌ፡ ድሬ፡ ሀረር፡ አዲስ አበባም ሆነ ሌሎች ከተሞች እንዳትደርስ ተባለ፡፡💔  የብሄር ብሄረሰቦች ሙዚቃን በአልበም ሲንግሎቹ ዘፍኗል፡፡ በየመድረኩም ለማቅረቡ የያኔዋ መቀሌ ትመሰክራለች፡፡ ከ 97 ጀምሮ ግን ይህ ሁሉ ተረስቶ የአሀዳዊ ስርአት ናፋቂ ተብሎ ተፈረጆም ነበር የክብር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ገርማሞ (ቴዲ አፍሮ)🙏 ያን በብዙ ታሪኩ የሚታወስ ኮንሰርት አስታከን ስለቴዲ ስናወሳ ደግሞ የዝግጅቱ ዋና ተዋንያን የነበሩትን አማኑኤል ይልማን፡ አህመድ ተፈራ፡ ገዛ ገርላሳን እና አብረዋቸው የነበሩትን በልዩነት ለማንሳትና ለማድነቅ ለማመስገን እንገደዳለን🙌🥰 ለዛሬ አበቃሁ። ክብር ለሚገባው ክብር እንሰጣለን🫡 musictube 🇪🇹 #fyp #ቴዲአፍሮ #ቀዘብዬ #ethiopianmusic #musictube369
'ቀዘብዬ'🌹🥹 ✨ውድ ቤተሰቦቼ ለመሆኑ ቴዲ አፍሮ በመቀሌ ህዝብ ከመወደዱ የተነሳ የኮንሰርት ቀን እንዲጨምር ተጠይቆ እንደነበር ታውቃላቹ?🤔 ዛሬ ለየት ባለ መልኩ ይሄንን በዳዊት መለሰ አበረታችነት ቴዲ አፍሮ ለሌሎች ሙዚቀኞች አዘጋጅቶት የነበሩትን ግጥም እና ዜማዎች አቧራቸውን አራግፎ ወደ ሙዚቃው ዘው ብሎ የገባበትትን ቀድሞ ቢሰራም በሁለተኛ አልበምነት ቴዎድሮስ ካሳሁን ብሎ በ94 ካሳተመው አልበም ላይ 'ቀዘብዬ'ን ጋብዣቹ የመቀሌው የ1994 ኮንሰርትና ባለሙያዎቹ ሲዘከሩ እንዲህ ነበር፡- ብለን አንድ የታሪክ ኩነት መዘን እናስታውሳለን🥰 ✍️ቴዲ 'አቦጊዳ' አልበሙን በ1993 መገባደጃ ላይ ይዞ ብቅ ሲል ቴዲ አፍሮ ማን ነው? የሚል ጥያቄ ጎረፈ፡፡ እድሜ ለኤፍኤም አዲስ 97.1 ዲጄዎችና የኪነጥበብ ፕሮግራም አዘጋጆች፡፡ እነ ዲጄ ዚ፣ አዲስ ዜማዎች፣ አይሬ፣ ዲጄ ኪን፣ አፍሪካ ጃዝ መንደርና ሌሎችም ደጋግመው ለህዝብ ስላስደመጡት ቴዲ በደንብ ከህዝብ ጋር መተዋወቅ ጀመረ፡፡ በዝነኛው የአለቤ ሾው ፕሮግራም ላይ ሲቀርብ ደግሞ ስሙ ናኘ፡፡ የቴዲ ተቀባይነት በጥቂት ወራቶች ከማንም በላይ ገዘፈ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር ከአቦጊዳ አልበም በፊት የሰራውና ለሙዚቃ አሳታሚ የሸጠው ጽጌረዳ/ቀዘብዬ የተባለው አልበሙ ሁለተኛ አልበም ተብሎ የተለቀቀው፡፡ በጊዜው ቴዲ አፍሮ የስራውን መለቀቅ ቢቃወምም ቀድሞ የሸጠው በመሆኑ ሙዚቃ አሳታሚው አልበሙን የማሰራጨት ሙሉ መብት ስለነበረው አለመግባባቱ በዛው ነበር የተቋጨው፡፡ ጽጌረዳ እንደ አቦጊዳ ባይሆንም ቴዲ አፍሮ ተደማጭነትና ዝናን አላጣም፡፡ በጽጌረዳ አልበም ውዝግብ ብቻ ሳይሆን የሴት ልጅ ጡት ላይ ፈረመ የሚሉ የማጥላላት ዘመቻዎች በሰፊው ተከፈተበት፡፡ ነገር ግን የያኔው የእሁድ ከሰአት የ 120 ቲቪ ፕሮግራም ላይ ቀርቦ አጥጋቢ መልስ በመስጠቱ ሁሉም በዛው ተደመደመ፡፡ ከነዚህ አልበሞች ተከታትሎ መለቀቅ በኋላ ቴዲ በአዲስ አበባና በየክልሉ እየዞረ ኮንሰርት ማቅረቡን ቀጠለ፡፡ የተለያዩ ፕሮሞተሮችና ፕሮዲዩሰሮች አይናቸውን ጣሉበት፡፡ በዚህ ወቅት ደግሞ ከዝነኛው የሙዚቃ አቀናባሪና የያኔው የኮንሰርት ፕሮሞተር አማኑኤል ይልማ ጋር ተገናኘ፡፡ ወጣቱ አቀናባሪና ፕሮሞተር አማኑኤል ይልማ መቀሌ ከተማ ላይ ደጋግሞ ኮንሰርቶችን ያሰራ ነበር፡፡ ዝነኛው የመቀሌ ከተማ ባህላዊ ባርና ሬስቶራንት ገዛ ገርላሳ ደግሞ ቤቱ ነበር፡፡ እዚህ ፈረንጅ የሚጎርፍበት ቤት ፍቅራዲስ ነቃጥበብን ሁለት ጊዜ የወሰደ ሲሆን ፍቅራዲስ አክሱም ጭምር ተሻግራ በተመሳሳይ ሰርታለች፡፡ ከአማኑኤል ጋር በመሆን ገዛ ገርላሳ ላይ እንደ ህብስት ጥሩነህ፣ ይርዳው ጤናው፣ ደረጀና ሀብቴ የመሳሰሉ አርቲስቶች ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በ 1994 ጥር 24 እና 25 ኮንሰርት ለማቅረብ ቀጠሮ የተያዘለት ባለተረኛ ደግሞ የጊዜው ባለዝነኛ ቴዲ አፍሮ ነበር፡፡ ይህን ኮንሰርት ለማቅረብ ለቴዲ አፍሮ 40 ሺህ ብር ሊከፈለው ተስማምቶ ለሁለት ቀናት ከአነ አማኑኤል ጋር ወደመቀሌ አቀኑ፡፡ የመቀሌ ህዝብ ቴዲ ባቀረበው ኮንሰርት እጅግ ተደሰተ፡፡ ነገር ግን ገዛ ገርላሳ በሁለት ቀናት ውስጥ ለመቀሌ ህዝብ ቴዲን ለማሳየት በቂ አልነበረም፡፡ በቦታ ጥበት ብዙዎች ኮንሰርቱ አመለጣቸው፡፡ በዚህ የተነሳ ቴዲ አንድ ቀን አድሮ ኮንሰርቱን እንዲሰራ ለእነ አማኑኤል የህዝብ ጥያቄ ጎረፈ፡፡ የመቀሌ ህዝብ ፍቅር ያሸነፈው ቴዲ ለጥያቄው አላመነታም፡፡ ለአንድ ተጨማሪ ቀን ኮንሰርቱን ለማራዘም ቴዲና አዘጋጆቹ ተስማሙ፡፡ ዝግጅቱ የተሳካና የተዋጣለት ሆኖ በዚሁ ተጠናቀቀ፡፡ ቴዲ አፍሮ በመቀሌ ቆይታው ለመቀሌ አድናቂዎቹ ያለውን በሙሉ ለመስጠትና ለማስደሰት ሞክሯል፡፡ ከሁለቱ አልበሞቹ ዘፈኖች በተጨማሪም አለምብሬ የተባለውን የጉራጊኛ ዘፈን ያቀረበ ሲሆን ኦሮሚኛ ዘፈን ጭምር ለህዝቡ ተጫውቷል፡፡ በትግርኛም መድረኩን አድምቋል፡፡ ደማቁ የዛን ጊዜው መድረክ ቴዲ አፍሮ ለሚወደው የመቀሌ ሙዚቃ አፍቃሪ ብዙ ደስታን የሰጠበትና ብዙ ፍቅር የሸመተበት ነበር፡፡ ይህ ከሆነ ከሶስት አመት በኀላ ቴዲ አፍሮ በያስተሰርያል አልበሙ ወደህዝብ ጆሮ ብቅ አለ፡፡ ስለሀገር ፍቅርና አንድነት በዘፈኖቹ የሰበከው ከያኒ ውለታው ተረስቶ ውግዝ ከማእርዮስ ተባለ፡፡ እየሩሳሌም ብሎ ለቅድስቲቱ ሀገር ሰላም ጮኸ፡ ቀነኒ ኬኛ ብሎ በአትሌቶቻችን የኦሎምፒክ ገድል የሀገር ፍቅር ቀሰቀሰ፡ ብዙዎችን በስሜት እምባ አራጨ፡ ቴዲ አፍሮ ወደሙዚቃው ከተቀላቀለ በኀላ ብዙ ባለተሰጥኦ ወጣቶች ፈለጉን ተከትለው መብቀል ጀመሩ፡፡ ይህ ሁሉ ግን 97 ላይ በዘፈነው ያስተሰርያል ተረሳ፡፡ መንግስት ዘፈኑ በማንኛውም ጣቢያ እንዳይደመጥ እቀባ ጣለ፡፡ ኢህአዴግ ልክ በግል እንደሚያሳድደው ደመኛው እግር በእግር እየተከታተለ ኮንሰርቱን ሰረዘበት፡፡ ቴዲ በሀገሩ ባይተዋር ተደረገ፡፡ ፍቅር የዘፈነባቸው መቀሌ፡ ድሬ፡ ሀረር፡ አዲስ አበባም ሆነ ሌሎች ከተሞች እንዳትደርስ ተባለ፡፡💔 የብሄር ብሄረሰቦች ሙዚቃን በአልበም ሲንግሎቹ ዘፍኗል፡፡ በየመድረኩም ለማቅረቡ የያኔዋ መቀሌ ትመሰክራለች፡፡ ከ 97 ጀምሮ ግን ይህ ሁሉ ተረስቶ የአሀዳዊ ስርአት ናፋቂ ተብሎ ተፈረጆም ነበር የክብር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ገርማሞ (ቴዲ አፍሮ)🙏 ያን በብዙ ታሪኩ የሚታወስ ኮንሰርት አስታከን ስለቴዲ ስናወሳ ደግሞ የዝግጅቱ ዋና ተዋንያን የነበሩትን አማኑኤል ይልማን፡ አህመድ ተፈራ፡ ገዛ ገርላሳን እና አብረዋቸው የነበሩትን በልዩነት ለማንሳትና ለማድነቅ ለማመስገን እንገደዳለን🙌🥰 ለዛሬ አበቃሁ። ክብር ለሚገባው ክብር እንሰጣለን🫡 musictube 🇪🇹 #fyp #ቴዲአፍሮ #ቀዘብዬ #ethiopianmusic #musictube369

About