@tornada_official: що тут за двіжуха #Tornada #Vovagel #gel

Tornada
Tornada
Open In TikTok:
Region: UA
Saturday 27 June 2026 15:35:18 GMT
23454
309
27
10

Music

Download

Comments

nicke_1991
𒄆NIK𒄆 :
2026-07-02 07:43:22
1
viktor.shimon8
Viktor Shimon :
🔥🔥🔥🔥
2026-06-30 17:12:45
1
user9923522517439
Nikola :
ніхуя собі
2026-06-30 13:52:01
0
denys_artist
🇺🇦 ~Denys_"ARTIST"~ 🇺🇦 :
с Юпитера буду😁😁😁
2026-06-27 15:37:48
1
melo_mo_od
Melo mood :
днб буду
2026-06-28 15:02:28
2
tornada_life
Tornada Life :
🔥🔥🔥
2026-06-27 19:57:09
1
kolydyw0q2u458wk
Nikolas Keug :
👍👍👍
2026-06-28 13:51:23
1
guannouch12345
GauN Nouch :
🥰🥰🥰
2026-06-29 11:17:35
1
_temphiot_
temphiot. :
😂😂😂
2026-06-27 19:39:00
1
petyapetrovpetrov
Петя Петров Петров :
😳😳😳
2026-06-29 18:56:21
2
andreymykhalcha
Andrey Mykhalcha :
🥰🥰🥰
2026-06-27 15:39:32
0
head_100hp
-100hp :
🔥🔥🔥
2026-07-01 15:53:02
1
andreymykhalcha
Andrey Mykhalcha :
🌹🌹🌹
2026-06-27 15:39:33
0
user123415980651
Василь Галіревич :
🥰🥰🥰
2026-06-27 15:45:29
0
nodari.vacheishvi
Nodari Vacheishvili :
🥰🥰🥰
2026-06-27 15:47:33
0
andreymykhalcha
Andrey Mykhalcha :
🔥🔥🔥
2026-06-27 15:39:29
0
userpgfqmaeqat
user30377895377 :
🥰🥰🥰🥰💪💪💪💪💪💪💪
2026-06-27 16:00:20
0
To see more videos from user @tornada_official, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

#ከምግብበፊትእናበኋላምንብለንእንጸልይ?  ከመመገባች በፊት ይህንን አባቶቻችን ከመዝሙረ ዳዊት አውጣጥተው የደረሱትን ጸሎት እናድርስ! «ለፍጥረት ሁሉ መልካም ነገርን የምትሠጥ አምላካችን እግዚአብሔር አንተ ምስጉን ነህ ስምህም የተመሰገነ ነው።  እኛም ስለ ፍጹም ሥጦታህ ፈጽመን እናመሰግንሃለን።  የፍጥረት ሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል። አንተ ለሁሉ በጊዜው ምግቡን ትሠጠዋለህና ቀኝህን ትዘረጋለህ ሁሉንም ታጠግባለህ። አሁንም ልዩ የሆነች ቀኝህን ዘርጋ ይህንን የሠጠኸንን ምግብና መጠጥም ባርክ ለሥጋችንና ለነፍሳችን ኃይልና ብርታት ይሆነን ዘንድ አንተ ቸር ታማኝ መጋቢ ነህና ለዘለዓለሙ አሜን! አባታችን ሆይ!» ግዕዝ:- («እግዚአብሔ አምላክነ ዘትሁብ ሠናያቲከ ለኩሉ ፍጥረት እኩት አንተ ወስቡሕ ስምከ ወንህነኒ ነአኩተከ ወንሴብሐከ በእንተ ፍጹም ጸጋከ ዓይነ ኩሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ  እስመ አንተ ትሁብ ሲሳየ ለኩሉ በጊዜሁ ትሰፍህ የማነከ ወታጸግብ ኩሎ ወይእዜኒ ስፋሕ የማነከ ቅድስተ ወባርክ ዘንተ መብልአ ወመስቴ ዘአስተዳለውከነ ከመ ይኩነነ ኃይለ ወጽንዓ ለሥ ጋነ ወነፍስነ እስመ አንተ ኄር ወምእመን መጋቤ ለዓለመ ዓለም አሜን! አቡነ ዘበሰማያት») . ከዚያም እንደየመዓርጉ መዓዱን የባረከው ሰው ለሌሎች ቆርሶ:- «በእንተ ማርያም በእንተ ኢየሱስ» እያለ ይሠጣል።  ቀሳውስት ደግሞ :- «በረከተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ» እያሉ ሲሰጡ :- ሰዉ «ይምጻእ ኀቤየ መንፈስ ቅዱስ» እያለ ይቀበላል።  ይህም ጌታችን በኤማሁስ አብረውት ሊበሉ ለተቀመጡት አርድእት እንደሰጣቸው በማየት የተሠራ ሥርዓት ነው። የመዓድ ጸሎት ትልቁ ጠቀሜታ ሰው ምንም ለጸሎት ጊዜ የለኝም ቢል እንኩዋን ለምግብ ጊዜ አጣሁ ሊል ስለማይችል በበላ ቁጥር እንዲጸልይ ያደርገዋል።  በቀን ሦስት ጊዜ የሚበላ ሰው ቢያንስ በቀን ሦስቴ ይጸልያል።  አቅሙ ቢችልና ለሥጋውም ሆነ ለነፍሱ ጤና ካልሰጋ በስተቀር አንድ ሰው በቀን ሰባት ጊዜ ቢበላ ሰባቱን የጸሎት ጊዜያት ጠነቀቀ ማለት ነው።  ጥቅሙን ለማስረዳት  ይህንን አመጣነው እንጂ ይህ እንኩዋን ለመብላት መጸለይ ሳይሆን ለመጸለይ መብላት ይሆናል። ከበላን በኋላ ስብሐት እንላለን።  በምንም ምክንያት ለመብላት ጊዜ እስካለን ድረስ ስብሐት ለማለትም ጊዜ መሥጠት አለብን። የበላነውን የጤና እንዲያደርግልንና እንዲስማማን ፣ እንዳያሳጣን ላጡትም እንዲያድላቸው ማመስገን ይገባል።  አንዳንድ ሰዎች «ምግቡ ከተረፈ ስብሐት አንልም ምክንያቱም ስብሐት ብንልበት ለውሻ ሊሠጥ ይችላል ፤ የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ ይላል።» ይላሉ።  ይህ ሃሳብ ግን ብዙ የማያስኬድና አንዳንዴም ለስንፍና ምክንያት ይሆናል። አንደኛ ስብሐት ከማለታችን በፊት ገና መብላት ስንጀምር ምግቡን በመባረካችን ምግቡ ከመነሻው የተባረከ ነው።  ሌላው ስብሐት የምንለው በመብላታችን ፈጣሪን ለማመስገን ነው እንጂ ባለማስተረፋችን አይደለም።  የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ የሚለውም ቃል ውሾችን ስላለመመገብ የተነገረ አይደለም። በደመ ነፍስ የሚኖሩት ምንም የማያውቁት እንስሳትስ ካለ እኛ ማን አላቸው?  ውሾች እኛ ያስተረፍነውን ሊበሉ አይገባም ማለት ከወንጌሉም ሃሳብ ጋር «ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ» ይላልና {ማቴ. 15፡27} እንዲያውም ከቅዱሳኑ የተማርነው ለውሾች ያስተረፍነውን መከልከል ሳይሆን ያልቀመስነውንም ከላዩ አንስተን መሥጠት እንዳለብን ነው።  ርኅርኅተ ኅሊና እመቤታችን ለውሻ የሰጠችው እስዋ እንኳን ሳትቀምሰው አጉድላ አልነበር? ጻድቅ ለእንስሳው ነፍስ ይራራል ይልስ የለ? ጌታ ሆይ የዕለት እንጀራችንን ስጠን ዛሬ፣ በደላችንንም ይቅር በለን!
#ከምግብበፊትእናበኋላምንብለንእንጸልይ? ከመመገባች በፊት ይህንን አባቶቻችን ከመዝሙረ ዳዊት አውጣጥተው የደረሱትን ጸሎት እናድርስ! «ለፍጥረት ሁሉ መልካም ነገርን የምትሠጥ አምላካችን እግዚአብሔር አንተ ምስጉን ነህ ስምህም የተመሰገነ ነው። እኛም ስለ ፍጹም ሥጦታህ ፈጽመን እናመሰግንሃለን። የፍጥረት ሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል። አንተ ለሁሉ በጊዜው ምግቡን ትሠጠዋለህና ቀኝህን ትዘረጋለህ ሁሉንም ታጠግባለህ። አሁንም ልዩ የሆነች ቀኝህን ዘርጋ ይህንን የሠጠኸንን ምግብና መጠጥም ባርክ ለሥጋችንና ለነፍሳችን ኃይልና ብርታት ይሆነን ዘንድ አንተ ቸር ታማኝ መጋቢ ነህና ለዘለዓለሙ አሜን! አባታችን ሆይ!» ግዕዝ:- («እግዚአብሔ አምላክነ ዘትሁብ ሠናያቲከ ለኩሉ ፍጥረት እኩት አንተ ወስቡሕ ስምከ ወንህነኒ ነአኩተከ ወንሴብሐከ በእንተ ፍጹም ጸጋከ ዓይነ ኩሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ እስመ አንተ ትሁብ ሲሳየ ለኩሉ በጊዜሁ ትሰፍህ የማነከ ወታጸግብ ኩሎ ወይእዜኒ ስፋሕ የማነከ ቅድስተ ወባርክ ዘንተ መብልአ ወመስቴ ዘአስተዳለውከነ ከመ ይኩነነ ኃይለ ወጽንዓ ለሥ ጋነ ወነፍስነ እስመ አንተ ኄር ወምእመን መጋቤ ለዓለመ ዓለም አሜን! አቡነ ዘበሰማያት») . ከዚያም እንደየመዓርጉ መዓዱን የባረከው ሰው ለሌሎች ቆርሶ:- «በእንተ ማርያም በእንተ ኢየሱስ» እያለ ይሠጣል። ቀሳውስት ደግሞ :- «በረከተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ» እያሉ ሲሰጡ :- ሰዉ «ይምጻእ ኀቤየ መንፈስ ቅዱስ» እያለ ይቀበላል። ይህም ጌታችን በኤማሁስ አብረውት ሊበሉ ለተቀመጡት አርድእት እንደሰጣቸው በማየት የተሠራ ሥርዓት ነው። የመዓድ ጸሎት ትልቁ ጠቀሜታ ሰው ምንም ለጸሎት ጊዜ የለኝም ቢል እንኩዋን ለምግብ ጊዜ አጣሁ ሊል ስለማይችል በበላ ቁጥር እንዲጸልይ ያደርገዋል። በቀን ሦስት ጊዜ የሚበላ ሰው ቢያንስ በቀን ሦስቴ ይጸልያል። አቅሙ ቢችልና ለሥጋውም ሆነ ለነፍሱ ጤና ካልሰጋ በስተቀር አንድ ሰው በቀን ሰባት ጊዜ ቢበላ ሰባቱን የጸሎት ጊዜያት ጠነቀቀ ማለት ነው። ጥቅሙን ለማስረዳት ይህንን አመጣነው እንጂ ይህ እንኩዋን ለመብላት መጸለይ ሳይሆን ለመጸለይ መብላት ይሆናል። ከበላን በኋላ ስብሐት እንላለን። በምንም ምክንያት ለመብላት ጊዜ እስካለን ድረስ ስብሐት ለማለትም ጊዜ መሥጠት አለብን። የበላነውን የጤና እንዲያደርግልንና እንዲስማማን ፣ እንዳያሳጣን ላጡትም እንዲያድላቸው ማመስገን ይገባል። አንዳንድ ሰዎች «ምግቡ ከተረፈ ስብሐት አንልም ምክንያቱም ስብሐት ብንልበት ለውሻ ሊሠጥ ይችላል ፤ የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ ይላል።» ይላሉ። ይህ ሃሳብ ግን ብዙ የማያስኬድና አንዳንዴም ለስንፍና ምክንያት ይሆናል። አንደኛ ስብሐት ከማለታችን በፊት ገና መብላት ስንጀምር ምግቡን በመባረካችን ምግቡ ከመነሻው የተባረከ ነው። ሌላው ስብሐት የምንለው በመብላታችን ፈጣሪን ለማመስገን ነው እንጂ ባለማስተረፋችን አይደለም። የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ የሚለውም ቃል ውሾችን ስላለመመገብ የተነገረ አይደለም። በደመ ነፍስ የሚኖሩት ምንም የማያውቁት እንስሳትስ ካለ እኛ ማን አላቸው? ውሾች እኛ ያስተረፍነውን ሊበሉ አይገባም ማለት ከወንጌሉም ሃሳብ ጋር «ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ» ይላልና {ማቴ. 15፡27} እንዲያውም ከቅዱሳኑ የተማርነው ለውሾች ያስተረፍነውን መከልከል ሳይሆን ያልቀመስነውንም ከላዩ አንስተን መሥጠት እንዳለብን ነው። ርኅርኅተ ኅሊና እመቤታችን ለውሻ የሰጠችው እስዋ እንኳን ሳትቀምሰው አጉድላ አልነበር? ጻድቅ ለእንስሳው ነፍስ ይራራል ይልስ የለ? ጌታ ሆይ የዕለት እንጀራችንን ስጠን ዛሬ፣ በደላችንንም ይቅር በለን!

About