@bienesalimenconc: Siente libre y protegida #destacados #espirulina #airiz #seguidores #tiensloja

TiensBienestarAlimentacionConc
TiensBienestarAlimentacionConc
Open In TikTok:
Region: EC
Monday 06 July 2026 22:10:54 GMT
120
6
0
4

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @bienesalimenconc, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በ94 ዓመታቸው ለናይጄሪያውያን ልብ የሚነካ ደብዳቤ ጽፈዋል።  ሰዎች ሕይወት ረጅም ናት ይላሉ፤ “ጊዜ አለህ፣ አትቸኩል” ይሉሃል። እኔ ግን አሁን የ94 ዓመት አረጋዊ ነኝ፤ በእርግጠኝነት ልነግራችሁ የምችለው ይህ ፍጹም ስህተት መሆኑን ነው።  ሕይወት ረጅም አይደለችም፤ በቅጽበት የምታልፍ እንጂ። ይህችን ዓለም የምሰናበትበት ጊዜ እየቀረበ ሲመጣ፣ ጥቂት የሕይወት ትምህርቶችን ላካፍላችሁ ወደድኩ። ሀብት አጋብሻለሁ፣ ተሰሚነትን አትርፌያለሁ፣ ታዋቂነትንም አግኝቻለሁ፤ ዛሬ ግን እነዚህ ሁሉ በቤቴ ጥግ ላይ እንደተከመረ ትቢያ ይቆጠራሉ። አሁን እጄን ብዘረጋ፣ ከእነዚህ መካከል አንዳቸውም አብረውኝ አይጓዙም። አንደኛ ትምህርት፦ ነገሮች እስኪስተካከሉ አትጠብቅ ከሕይወቴ አብዛኛውን ክፍል ያሳለፍኩት በመጠበቅ ነበር። በትምህርት ቤት እያለሁ፣ እውነተኛው ሕይወት የሚጀምረው ከምረቃ በኋላ ይመስለኝ ነበር። ውትድርና ውስጥ በነበርኩበት ጊዜ፣ ቅዳሜና እሁድን እጓጓ ነበር። ትዳር ስመሰርት፣ ልጆቼ እስኪያድጉ እጠብቅ ነበር። እነሱ ሲያድጉ ደግሞ፣ ጡረታ የምወጣበትን ጊዜ መናፈቅ ጀመርኩ። እውነተኛው ሕይወት ወደፊት መቼም ያለ ይመስል፣ እያንዳንዱን ቀን እንደ ተራ መሻገሪያ ድልድይ ብቻ ነው ያየሁት። አሁን ግን ተረዳሁ፤ ሕይወት ማለት የመጨረሻው መድረሻ ሳትሆን፣ እራሱ አሁን የምንጓዘው ጉዞ ናት። ሁለተኛ ትምህርት፦ ወርቅ ምግብ አይሆንም ሀብት ለማከማቸት 50 ዓመታት ሙሉ ደክሜያለሁ። ሥራ ላይ ከማተኮሬ የተነሳ ከቤተሰቤ ጋር የማሳልፋቸውን ውድ ጊዜያት አጥቻለሁ። ትላልቅ ቤቶችን፣ ውድ መኪናዎችንና የቅንጦት ዕቃዎችን ገዝቻለሁ፤ ነገር ግን የጉዞዬ ማብቂያ ላይ ስቃረብ፣ ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም ሊከተሉኝ እንደማይችሉ ተገነዘብኩ። አንድ ቀን ልጄ ያገኘችውን አንዲት ጥቃቅን ነፍሳት እንዳይላት ወደ አትክልት ስፍራው የጠራችኝ ዕለት ሁሌም ትዝ ይለኛል።  እኔ ግን “አሁን አልችልም፣ ሥራ ላይ ነኝ” አልኳት።  ያንን ያመለጠኝን አፍታ ሳስብ እስከ ዛሬ ድረስ ቁጭቱ ይብሰኛል። ሦስተኛ ትምህርት፦ በልብህ ውስጥ ያለውን ግንብ አፍርስ በወጣትነቴ መራራት ወይም ይቅርታ መጠየቅ የድክመት ምልክት ይመስለኝ ነበር።  አንድ ወንድም ነበረኝ። አንድ ቀን በትንሽ ነገር ተጣላን፤ እንዲያውም ጠቡ በምን እንደተጀመረ አሁን ላይ ትዝ እንኳን አይለኝም። እሱ መጥቶ ሰላም እስኪለኝና እስክንታረቅ ድረስ እልህ ይዤ ጠበቅኩ። ዓመታት አለፉ።  ከዚያም በአንድ ወቅት፣ እሱ ማረፉን የሚገልጽ የስልክ ጥሪ ደረሰኝ። ያኔ ነው እኔ ትክክል ብሆንም፣ ወንድሜን ግን ለዘላለም እንዳጣሁት የተረዳሁት። የምትወዱት ሰው ካለ፣ ዛሬውኑ ንገሩት። ስህተት ሠርታችሁ ከሆነ፣ ዛሬውኑ ይቅርታ ጠይቁ። ነገ ለማንኛችንም ዋስትና የለውም። አራተኛ ትምህርት፦ ፍርሃት ጥላ ብቻ ነው ደራሲ ለመሆን ስመኝ ዕድሜዬ 22 ዓመት ነበር። ማስታወሻዎቼ በሕልሞችና በታሪኮች የተሞሉ ነበሩ። ነገር ግን ሰዎች ይሳቁብኛል ወይም አልቀናኝም በሚል ፍርሃት ያንን መጽሐፍ ሳልጽፈው ቀረሁ።አሁን እጆቼ ይንቀጠቀጣሉ፣ ዓይኖቼም ፈዝዘዋል። ያ መጽሐፍ ግን አሁንም በውስጤ እንዳለ ቀርቷል። በሕይወት ውስጥ ትልቁ አሳዛኝ ነገር ሞት አይደለም፤ በሕይወት እያለን ቀብረናቸው የምንቀራቸው ሕልሞቻችን እንጂ። ልባችሁ የሚፈልገውን ነገር ወደፊት አታስተላልፉት። ዛሬውኑ ጀምሩ።  ባይሳካላችሁ እንኳ፣ ቢያንስ “ሞክሬው ነበር” ማለት ትችላላችሁ። የዘመኔ ሰዓት የምታሰማው ድምፅ አሁን በጆሮዬ ላይ እየጎላ መጥቷል። ጭንቀትን፣ ኩራትንና ፍርሃትን ሁሉ አውርጄ ጥያለሁ። እናንተ ግን አሁንም በሕይወት አላችሁ። ሌላ አዲስ ቀን ተሰጥቷችኋል። በከንቱ አታባክኑት። እጆቻችሁን እዩ። ጣቶቻችሁን አንቀሳቅሱ። የአተነፋፈሳችሁን ምት ስሙ።ይህ ሁሉ ትልቅ በረከት ነው። ሕይወት ምን ያህል ውብ መሆኗን ለመረዳት 94 ዓመት እስኪሞላችሁ ድረስ አትጠብቁ።አሁንን ኑሩት።  via Hassen Mustefa
ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በ94 ዓመታቸው ለናይጄሪያውያን ልብ የሚነካ ደብዳቤ ጽፈዋል። ሰዎች ሕይወት ረጅም ናት ይላሉ፤ “ጊዜ አለህ፣ አትቸኩል” ይሉሃል። እኔ ግን አሁን የ94 ዓመት አረጋዊ ነኝ፤ በእርግጠኝነት ልነግራችሁ የምችለው ይህ ፍጹም ስህተት መሆኑን ነው። ሕይወት ረጅም አይደለችም፤ በቅጽበት የምታልፍ እንጂ። ይህችን ዓለም የምሰናበትበት ጊዜ እየቀረበ ሲመጣ፣ ጥቂት የሕይወት ትምህርቶችን ላካፍላችሁ ወደድኩ። ሀብት አጋብሻለሁ፣ ተሰሚነትን አትርፌያለሁ፣ ታዋቂነትንም አግኝቻለሁ፤ ዛሬ ግን እነዚህ ሁሉ በቤቴ ጥግ ላይ እንደተከመረ ትቢያ ይቆጠራሉ። አሁን እጄን ብዘረጋ፣ ከእነዚህ መካከል አንዳቸውም አብረውኝ አይጓዙም። አንደኛ ትምህርት፦ ነገሮች እስኪስተካከሉ አትጠብቅ ከሕይወቴ አብዛኛውን ክፍል ያሳለፍኩት በመጠበቅ ነበር። በትምህርት ቤት እያለሁ፣ እውነተኛው ሕይወት የሚጀምረው ከምረቃ በኋላ ይመስለኝ ነበር። ውትድርና ውስጥ በነበርኩበት ጊዜ፣ ቅዳሜና እሁድን እጓጓ ነበር። ትዳር ስመሰርት፣ ልጆቼ እስኪያድጉ እጠብቅ ነበር። እነሱ ሲያድጉ ደግሞ፣ ጡረታ የምወጣበትን ጊዜ መናፈቅ ጀመርኩ። እውነተኛው ሕይወት ወደፊት መቼም ያለ ይመስል፣ እያንዳንዱን ቀን እንደ ተራ መሻገሪያ ድልድይ ብቻ ነው ያየሁት። አሁን ግን ተረዳሁ፤ ሕይወት ማለት የመጨረሻው መድረሻ ሳትሆን፣ እራሱ አሁን የምንጓዘው ጉዞ ናት። ሁለተኛ ትምህርት፦ ወርቅ ምግብ አይሆንም ሀብት ለማከማቸት 50 ዓመታት ሙሉ ደክሜያለሁ። ሥራ ላይ ከማተኮሬ የተነሳ ከቤተሰቤ ጋር የማሳልፋቸውን ውድ ጊዜያት አጥቻለሁ። ትላልቅ ቤቶችን፣ ውድ መኪናዎችንና የቅንጦት ዕቃዎችን ገዝቻለሁ፤ ነገር ግን የጉዞዬ ማብቂያ ላይ ስቃረብ፣ ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም ሊከተሉኝ እንደማይችሉ ተገነዘብኩ። አንድ ቀን ልጄ ያገኘችውን አንዲት ጥቃቅን ነፍሳት እንዳይላት ወደ አትክልት ስፍራው የጠራችኝ ዕለት ሁሌም ትዝ ይለኛል። እኔ ግን “አሁን አልችልም፣ ሥራ ላይ ነኝ” አልኳት። ያንን ያመለጠኝን አፍታ ሳስብ እስከ ዛሬ ድረስ ቁጭቱ ይብሰኛል። ሦስተኛ ትምህርት፦ በልብህ ውስጥ ያለውን ግንብ አፍርስ በወጣትነቴ መራራት ወይም ይቅርታ መጠየቅ የድክመት ምልክት ይመስለኝ ነበር። አንድ ወንድም ነበረኝ። አንድ ቀን በትንሽ ነገር ተጣላን፤ እንዲያውም ጠቡ በምን እንደተጀመረ አሁን ላይ ትዝ እንኳን አይለኝም። እሱ መጥቶ ሰላም እስኪለኝና እስክንታረቅ ድረስ እልህ ይዤ ጠበቅኩ። ዓመታት አለፉ። ከዚያም በአንድ ወቅት፣ እሱ ማረፉን የሚገልጽ የስልክ ጥሪ ደረሰኝ። ያኔ ነው እኔ ትክክል ብሆንም፣ ወንድሜን ግን ለዘላለም እንዳጣሁት የተረዳሁት። የምትወዱት ሰው ካለ፣ ዛሬውኑ ንገሩት። ስህተት ሠርታችሁ ከሆነ፣ ዛሬውኑ ይቅርታ ጠይቁ። ነገ ለማንኛችንም ዋስትና የለውም። አራተኛ ትምህርት፦ ፍርሃት ጥላ ብቻ ነው ደራሲ ለመሆን ስመኝ ዕድሜዬ 22 ዓመት ነበር። ማስታወሻዎቼ በሕልሞችና በታሪኮች የተሞሉ ነበሩ። ነገር ግን ሰዎች ይሳቁብኛል ወይም አልቀናኝም በሚል ፍርሃት ያንን መጽሐፍ ሳልጽፈው ቀረሁ።አሁን እጆቼ ይንቀጠቀጣሉ፣ ዓይኖቼም ፈዝዘዋል። ያ መጽሐፍ ግን አሁንም በውስጤ እንዳለ ቀርቷል። በሕይወት ውስጥ ትልቁ አሳዛኝ ነገር ሞት አይደለም፤ በሕይወት እያለን ቀብረናቸው የምንቀራቸው ሕልሞቻችን እንጂ። ልባችሁ የሚፈልገውን ነገር ወደፊት አታስተላልፉት። ዛሬውኑ ጀምሩ። ባይሳካላችሁ እንኳ፣ ቢያንስ “ሞክሬው ነበር” ማለት ትችላላችሁ። የዘመኔ ሰዓት የምታሰማው ድምፅ አሁን በጆሮዬ ላይ እየጎላ መጥቷል። ጭንቀትን፣ ኩራትንና ፍርሃትን ሁሉ አውርጄ ጥያለሁ። እናንተ ግን አሁንም በሕይወት አላችሁ። ሌላ አዲስ ቀን ተሰጥቷችኋል። በከንቱ አታባክኑት። እጆቻችሁን እዩ። ጣቶቻችሁን አንቀሳቅሱ። የአተነፋፈሳችሁን ምት ስሙ።ይህ ሁሉ ትልቅ በረከት ነው። ሕይወት ምን ያህል ውብ መሆኗን ለመረዳት 94 ዓመት እስኪሞላችሁ ድረስ አትጠብቁ።አሁንን ኑሩት። via Hassen Mustefa

About