@abc_info1: ሰበር መረጃ 🚫 በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ በአንቀጽ 39 ዙሪያ መግባባት ላይ አለመደረሱ ተገለጸ:: ​በይፋ ከተከፈተ አንድ ሳምንት ባስቆጠረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ላይ ተሳታፊዎች በስምንት ዋነኛ አጀንዳዎች ዙሪያ እየተወያዩ ይገኛሉ። “የመንግስት አደረጃጀት እና ቅርጽ” እንዲሁም “የፖለቲካ ስርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ስርዓት” ከዋነኞቹ አጀንዳዎች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን፤ በእነዚህ ስር ከተያዙ ንዑስ ጉዳዮች መካከል የኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 39 አንዱ ነው። ​የቁጫ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቁህዴፓ) ተወካይ አቶ ባንዲራ በላቸው እንደገለጹት፤ “የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከ መገንጠል” መብትን በሚደነግገው በዚህ አንቀጽ ዙሪያ በተሳታፊዎች ዘንድ አለመግባባት ተፈጥሯል። ​በውይይቱ ወቅት አንቀጹ “ይነሳ” የሚሉ ወገኖች እንዳሉ ሁሉ፤ “የማንነት፣ የቋንቋ እና የዜጎች መብት ዋስትና በመሆኑ አይነሳ” የሚሉ ሀሳቦች መነሳታቸውንና እስካሁንም መግባባት ላይ አለመደረሱን ተወካዩ አስረድተዋል። #viral #fyp #foryou #viralvideo #viralvideo @Dr.no/Beyaynet-innovations @Meti_Breaking🥶

ABC info.
ABC info.
Open In TikTok:
Region: ET
Thursday 23 July 2026 18:48:14 GMT
5718
139
2
12

Music

Download

Comments

belete0529
belete ቁጫው 🇺🇾🇺🇾🇺🇾ሺጫው :
2026-07-24 07:36:19
0
birgen456
gen3567 :
ግዜን በማይሆን ነገር መግደል ተገቢ አይደለም።የአዲስ አበባ ጉዳይ መታየቱ ባይከፋም ጉዳዩ በአዲስ አበባ ህዝብ በወሰን ። ዋና ዋና ነገሮች 1. በሁሉም ደረጃ የስልጣን ገደብ በአመት የተወሰነ ይኑር። በተለይ የላይኛው 2. ህገ መንግስቱ ላይ ሰውን እንደ ዜጋ ይይ 3. አጀንዳዎቹ: አሁንም ይጥራ፣ ለምሳሌ ሙስና በግልፃ የሚደግፍ ዜጋ የለም። ስለዚህ ይህ በዚህ ውይይት ማውራት አያስፈልግም፣ 4. አሁን አሁን የመጣ ነገር ደግም፣ አስፈፃሚው የመንግስት አካል በከንቲባ ቢሮ እና በወረዳ የዳኝነት አገልግሎት ካልሰጠሁ ይላል፡፡ ስለዚህ የ 3ቱ የመንግስት ክፍሎች ድንበራቸው መታወቅ አለበት 5. መከላከያ ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሆን አለበት። ጠ/ሚንስቴር መከላከያን በቀጥታ ማዘዝ ባይችሉ፧፧ 6. የክልል ወስን ጉዳይ 7. ፌደራል ፖሊስ ተጠሪነቱ ለ ህግ ተርጓሚ የመንግስት አካል ቢሆን 8. ሪፐሊካን ጋርድ ተጠሪነቱ ለህግ አስፈፃሚ አካል ቢሆን
2026-07-23 19:29:47
1
To see more videos from user @abc_info1, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos


About