@melancholic962:

melancholic
melancholic
Open In TikTok:
Region: UA
Tuesday 28 July 2026 14:25:19 GMT
45
10
0
1

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @melancholic962, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

#ኤልያስ_ሽታኹን  ናፍቆት ስንት ይፈጃል? ያረጃል? ወይስ ያስረጃል? ይገላል ወይስ ያስገልላል? ናፍቆት ምን ያህላል? መንበረስላሴን ወይንስ ስላሴን ነገረሕይወትን ወይስ የሰው ሞትን የቀጣፊን ምላስ ወይ የሳራን ዳስ የጋሽ ጥላሁንን የረዘመ ትንፋሽ  ማንን ነው ሚያክለው? በናፍቆት የከፋኝ በናፍቆት የከፋሽ:: እኔና አንቺ እኮ እናሳዝናለን፡፡ መነፋፈቅ መርገም  ክብራችን መለገም የት ያደርስን እንደሁ ባናውቀውም እንጃ ሰው ከራስ ሲጣላ የት ይኬዳል ምልጃ? እንጃ፡፡ የመናፈቅ መቅሰፍት  አልፎ ላያልፍልን ያልቅብን ይመስል ገላ ተካፈልን ሰቀልነው   ገረፍነው   ገደልነው   ቀበርነው  የኔና አንቺ ፍቅር እሁድ ለሊት ያው ነው፡፡  መቃብር አይከፍትም ከፈኑን አይቀድም የኔና አንቺ ፍቅር ትንቢትን አይወድም፡፡ ለወሬ ለዓለም  አልተረፈምና ነገርና ስሙ አረገ አይባል መላዕክት አልሰሙ፡፡ (የት ገባ ይባላል?) ቀረ በነበረ በነበረ ቀረ:: እንደተነፋፈቅን እንደተጠባበቅን በሌለ ሰው ናፍቆት እንደተቃጠረ በሰነፍ ኮረዳ እንደተበጠረ የትም ተበተነ  የትም ቦታ ቀረ (የኔና አንቺ ፍቅር) መቃጠል እጣው ነው በፍም የታጠረ፡፡ መናፈቅ መፈለግ ስንት ህመም ያድላል? ከስንቱ ያውላል? በስንቱ ያስማል? በስንቱ ያስምላል? ተጠባብቀን ያለቀን  መዓት ቢፍለቀለቅ እኔና አንቺ ላንላቀቅ  በቀረን እንደሀውልት ደርቀን  እስከጌታ ፍርድ ቀን ስንቱን አወጣሁኝ ስንቱን አወረድኩኝ? ስንቱን ቀባጠርኩኝ? ናፈቀሽኝ ስንት ሆንኩኝ ? ቀጥረሽኝ በቆሞኩኝ፡፡ ሰበብ በሆንሽልኝ ቀጥራኛለች ብዬ ሸማ ባዘዝኩልሽ ለክር ሸሜኔ ቀሚስሽ እስኪደርስ ባለቀ ዘመኔ፡፡ ሰበብ በሆንሽልኝ  ቀጥራው ቀረች ብሎ ሰው በኔ እስኪያማሽ መቃብር መግባቴን አግብተሽ በሰማሽ፡፡ መናፈቅ እንደልጅ እያንቀለቀለኝ እንደሽማግሌ በቀኔ ገደለኝ፡፡  እንደጠዋት ፀሀይ አሰኘኝ ልሞቅሽ እንደአድባር ስለት ስለቴ ባረግሽ፡፡ እንደእናት ምርቃት ባልኩሽ አሜን አሜን አቤት ስል በኖርኩኝ ሆነሽ ቅፅል ስሜን፡፡ ናፈቀሽኝ  ናፈቀሽኝ እኔና እንቺኮ እናሳዝናለን፡፡ እየተዋደደድን  እየተፋቀረን መች አንድ ላይ አለን? እናሳዝናለን፡፡ *     *     *      *     *    *     *      *      *     * #ግጥም_በግጥም #viral #foryou #ግጥም
#ኤልያስ_ሽታኹን ናፍቆት ስንት ይፈጃል? ያረጃል? ወይስ ያስረጃል? ይገላል ወይስ ያስገልላል? ናፍቆት ምን ያህላል? መንበረስላሴን ወይንስ ስላሴን ነገረሕይወትን ወይስ የሰው ሞትን የቀጣፊን ምላስ ወይ የሳራን ዳስ የጋሽ ጥላሁንን የረዘመ ትንፋሽ ማንን ነው ሚያክለው? በናፍቆት የከፋኝ በናፍቆት የከፋሽ:: እኔና አንቺ እኮ እናሳዝናለን፡፡ መነፋፈቅ መርገም ክብራችን መለገም የት ያደርስን እንደሁ ባናውቀውም እንጃ ሰው ከራስ ሲጣላ የት ይኬዳል ምልጃ? እንጃ፡፡ የመናፈቅ መቅሰፍት  አልፎ ላያልፍልን ያልቅብን ይመስል ገላ ተካፈልን ሰቀልነው  ገረፍነው  ገደልነው  ቀበርነው የኔና አንቺ ፍቅር እሁድ ለሊት ያው ነው፡፡ መቃብር አይከፍትም ከፈኑን አይቀድም የኔና አንቺ ፍቅር ትንቢትን አይወድም፡፡ ለወሬ ለዓለም  አልተረፈምና ነገርና ስሙ አረገ አይባል መላዕክት አልሰሙ፡፡ (የት ገባ ይባላል?) ቀረ በነበረ በነበረ ቀረ:: እንደተነፋፈቅን እንደተጠባበቅን በሌለ ሰው ናፍቆት እንደተቃጠረ በሰነፍ ኮረዳ እንደተበጠረ የትም ተበተነ የትም ቦታ ቀረ (የኔና አንቺ ፍቅር) መቃጠል እጣው ነው በፍም የታጠረ፡፡ መናፈቅ መፈለግ ስንት ህመም ያድላል? ከስንቱ ያውላል? በስንቱ ያስማል? በስንቱ ያስምላል? ተጠባብቀን ያለቀን መዓት ቢፍለቀለቅ እኔና አንቺ ላንላቀቅ በቀረን እንደሀውልት ደርቀን እስከጌታ ፍርድ ቀን ስንቱን አወጣሁኝ ስንቱን አወረድኩኝ? ስንቱን ቀባጠርኩኝ? ናፈቀሽኝ ስንት ሆንኩኝ ? ቀጥረሽኝ በቆሞኩኝ፡፡ ሰበብ በሆንሽልኝ ቀጥራኛለች ብዬ ሸማ ባዘዝኩልሽ ለክር ሸሜኔ ቀሚስሽ እስኪደርስ ባለቀ ዘመኔ፡፡ ሰበብ በሆንሽልኝ ቀጥራው ቀረች ብሎ ሰው በኔ እስኪያማሽ መቃብር መግባቴን አግብተሽ በሰማሽ፡፡ መናፈቅ እንደልጅ እያንቀለቀለኝ እንደሽማግሌ በቀኔ ገደለኝ፡፡ እንደጠዋት ፀሀይ አሰኘኝ ልሞቅሽ እንደአድባር ስለት ስለቴ ባረግሽ፡፡ እንደእናት ምርቃት ባልኩሽ አሜን አሜን አቤት ስል በኖርኩኝ ሆነሽ ቅፅል ስሜን፡፡ ናፈቀሽኝ ናፈቀሽኝ እኔና እንቺኮ እናሳዝናለን፡፡ እየተዋደደድን እየተፋቀረን መች አንድ ላይ አለን? እናሳዝናለን፡፡ *     *     *      *     *    *     *      *      *     * #ግጥም_በግጥም #viral #foryou #ግጥም

About