@byrickytorres_27: la gloria sea para ti señor 🙏🏻❤️❤️#pequeñoturbo #parati #byrickytorres

#byrickytorres
#byrickytorres
Open In TikTok:
Region: CO
Sunday 02 August 2026 01:27:57 GMT
659
12
0
3

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @byrickytorres_27, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

ይህ ቃል ያስደነግጠኛል 😭! ​እናንተስ ምን  ያስደነግጣችኋል? ሞት ነውን? ይሄማ ከሞት በኋላ ሕይወት መኖሩን ለማያምኑት ነው። ረሀብ ወይስ ስደት? ይህማ “ስለ ጽድቅ የሚራቡ ብጹዓን ናቸው ይጠግባሉና” (ማቴ. 5፥6) የሚለውን ቃል ኪዳን ለዘነጉት ነው። ​እኔ ግን ሳስበውም ሆነ ሳነበው መላ አካላቴን የሚያንቀጠቅጠኝና የሚያስደነግጠኝ የጌታ የፍርድ ቃል ነው፦ ​“የማይጠቅም ይህንን ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል!” (ማቴ. 25፥30) 😭 ​ይህ ሰው መክሊቱን መቅበሩ ብቻ ሳይሆን፣ ለፈጣሪው ያለው ንቀትና እብሪት ያስፈራል። ለገዛ ስንፍናው እግዚአብሔርን ተጠያቂ እያደረገ “ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ” (ማቴ. 25፥25) እያለ ይከራከራል። ​ኦ ጌታ ሆይ! እኛስ ምን ይሻለናል? 💔 የተራቡትን አይተን እንዳላየን ያለፍነው፣ በእጃችን ያስቀመጥከውን መክሊትህን መቅበራችን መሆኑን ዘንግተን ነው። 💔 ምጽዋት የሚጠይቁንን ቸል ያልናቸው፣ በእጃችን ያለው ጸጋ ያንተ መሆኑን ረስተን የራሳችን ስለመሰለን ነው። 💔 የተረፈንን እንጀራ እንኳን ለድሆች እንዳይተርፍ እጃችንን የምንጠርግ ግፈኞች ነን። ድሆች በደጃችን ሲያለቅሱ፣ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት የዘለዓለም እሳት ሊጥለን የሚችል ታላቅ ጌታ እንዳላቸው እንዴት ዘነጋን? 😭 ​ጌታ ሆይ! በአፋችን ስንፍና ልክ አትፍረድብን። ፍሬ ያጣችባትን በለስ ለአንድ ዓመት ታግሰህ ዕድል እንደሰጠሃት፣ ለኛም ዕድል ስጠን! ምናልባት ለከርሞ ብንጠቅም... “ይህን የማይጠቅም ባሪያ አውጡት” ብለህ እንዳትፈርድብን እንማጸንሃለን!  ​እናንተስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነፍሳችሁን የሚያስደነግጣት ቃል የትኛው ነው? ከታች በኮሜንት ጻፉልኝ። ​ ወንድማችሁ ግርማ ይመር ነኝ ​#የእግዚአብሔርፍርድ #ንስሀእንግባየኦርቶዶክስልጆች   #የነፍስምግብ #ሀይማኖትአንዲትናት #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ፀንታ_ለዘለዓለም_ትኑር
ይህ ቃል ያስደነግጠኛል 😭! ​እናንተስ ምን  ያስደነግጣችኋል? ሞት ነውን? ይሄማ ከሞት በኋላ ሕይወት መኖሩን ለማያምኑት ነው። ረሀብ ወይስ ስደት? ይህማ “ስለ ጽድቅ የሚራቡ ብጹዓን ናቸው ይጠግባሉና” (ማቴ. 5፥6) የሚለውን ቃል ኪዳን ለዘነጉት ነው። ​እኔ ግን ሳስበውም ሆነ ሳነበው መላ አካላቴን የሚያንቀጠቅጠኝና የሚያስደነግጠኝ የጌታ የፍርድ ቃል ነው፦ ​“የማይጠቅም ይህንን ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል!” (ማቴ. 25፥30) 😭 ​ይህ ሰው መክሊቱን መቅበሩ ብቻ ሳይሆን፣ ለፈጣሪው ያለው ንቀትና እብሪት ያስፈራል። ለገዛ ስንፍናው እግዚአብሔርን ተጠያቂ እያደረገ “ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ” (ማቴ. 25፥25) እያለ ይከራከራል። ​ኦ ጌታ ሆይ! እኛስ ምን ይሻለናል? 💔 የተራቡትን አይተን እንዳላየን ያለፍነው፣ በእጃችን ያስቀመጥከውን መክሊትህን መቅበራችን መሆኑን ዘንግተን ነው። 💔 ምጽዋት የሚጠይቁንን ቸል ያልናቸው፣ በእጃችን ያለው ጸጋ ያንተ መሆኑን ረስተን የራሳችን ስለመሰለን ነው። 💔 የተረፈንን እንጀራ እንኳን ለድሆች እንዳይተርፍ እጃችንን የምንጠርግ ግፈኞች ነን። ድሆች በደጃችን ሲያለቅሱ፣ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት የዘለዓለም እሳት ሊጥለን የሚችል ታላቅ ጌታ እንዳላቸው እንዴት ዘነጋን? 😭 ​ጌታ ሆይ! በአፋችን ስንፍና ልክ አትፍረድብን። ፍሬ ያጣችባትን በለስ ለአንድ ዓመት ታግሰህ ዕድል እንደሰጠሃት፣ ለኛም ዕድል ስጠን! ምናልባት ለከርሞ ብንጠቅም... “ይህን የማይጠቅም ባሪያ አውጡት” ብለህ እንዳትፈርድብን እንማጸንሃለን! ​እናንተስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነፍሳችሁን የሚያስደነግጣት ቃል የትኛው ነው? ከታች በኮሜንት ጻፉልኝ። ​ ወንድማችሁ ግርማ ይመር ነኝ ​#የእግዚአብሔርፍርድ #ንስሀእንግባየኦርቶዶክስልጆች   #የነፍስምግብ #ሀይማኖትአንዲትናት #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ፀንታ_ለዘለዓለም_ትኑር

About