@amhara.agriculture: በአማራ ክልል ከ327 ሚሊዮን በላይ ችግኞች የሚተከሉበት የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ክቡር ከቲባ ጎሹ እዳላመው በተገኙበት ተካሄደ ባህርዳር ፣ ሃምሌ 27/2018 ዓ.ም ( ግብርና ቢሮ ) በአማራ ክልል በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ዘዘልማ ቀበሌ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል 8ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በታላቅ ንቅናቄ መካሄዱን ክቡር ከቲባ ጎሹ እዳላመው ተናግረዋል። በቦታው ተገኝተው መርሃ ግብሩን አስጀምረው ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል ግብርና ምክትል ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ መሰሉ ብርሃኑ እንደገለጹት፤ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የአፈርና ውኃ ጥበቃን ለማጠናከር እንዲሁም የከፋውን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመቋቋም ከፍተኛ ሚና አለው። ኃላፊዋ አክለውም በቅድሚያ ትኩረት ከተሰጣቸው ተክሎች መካከል ለምግብነት የሚያገለግሉ የፍራፍሬ ችግኞችና ለአፈር ጥበቃ የሚረዱ ተክሎች በግንባር ቀደምትነት እንደሚገኙበት አብራርተዋል። በዕለቱም በክልሉ ደረጃ በአንድ ጀምበር ብቻ በ65 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ላይ ከ327 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ይተከላሉ ተብሎ ይታሰባል ሲሉ ጠቁመዋል። ሃላፊዋ አጽንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት፤ "የመርሃ ግብሩ ዋና ግብ ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን የተተከሉትን ተክሎች በጥንቃቄ መንከባከብ፣ ማጽደቅና ለፍሬ ማብቃት ነው" ብለዋል። አረንጓዴ አሻራን ማሳረፍ የተፈጥሮ ሀብትን ጠብቆ ለነገዋ ኢትዮጵያና ለወደፊቱ ትውልድ የማስተላለፊያ ዋነኛ መንገድ መሆኑንም ገልጸዋል። በዚሁ ታላቅ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ አርሶ አደሮች፣ ወጣቶች፣ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም መላው የክልሉ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ ተሳትፏል። ዘጋቢ : አሻግረው ፈረደ ፎቶ : ጌታቸው ታፈረ #ተስፋን_እንትከል #የአማራ_ክልል_ግብርና_ቢሮ #ግብርና_ከማምረትም_በላይ_ነው #agricultur #agri

Amhara Agriculture Bureau
Amhara Agriculture Bureau
Open In TikTok:
Region: ET
Monday 03 August 2026 07:18:50 GMT
1226
49
1
65

Music

Download

Comments

abay8519
abay :
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️👍👍👍
2026-08-03 11:06:29
0
To see more videos from user @amhara.agriculture, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos


About