@fluxo.aep1: Aegon and Sunfyre back together🗿🐉#houseofthedragon #aegontargaryen #houseofthedragonedit #fyp #dragons

fluxo.aep
fluxo.aep
Open In TikTok:
Region: SE
Monday 03 August 2026 12:35:29 GMT
49510
6215
103
173

Music

Download

Comments

kuzminaoks
user9172069112430 :
Beautiful king 👑
2026-08-06 06:40:19
0
s0me0ne40k
Real Cop :
The tears in his eyes🥺
2026-08-06 03:47:16
1
templarotter
templarotter :
Sunfyre on his way to have one of the best kill count of the show
2026-08-04 08:04:40
11
silkandspindle
Silk & Spindle :
unpopular opinion, Aegon was a much better monarch than Rhaenyra. He genuinely wanted the smallfolk on side, and was lobbying for Harrenhall. He desperately wanted to be loved once he found a purpose. Justice for my King!
2026-08-04 11:51:00
5
lxsamre
𝓉𝒽𝑒 𝑔𝑜𝓁𝒹𝑒𝓃 :
2026-08-03 17:37:17
42
p_benim
𝘽𝙚𝙭𝙡𝙚𝙮🥷🏻:) :
the laugh of Aegon 🔥
2026-08-03 13:59:52
13
arnaldinho1089
arnaldinho1089 :
Aegon já fez mais do que Rhaenyra!!!
2026-08-04 03:11:55
10
jap1nesa2
Siyuzii :
The question is, how is Sunfyre alive?
2026-08-03 20:19:47
6
zamantha.1416
zamantha.MB :
Los dos quedaron igual de jod**os jajajjajaj
2026-08-03 21:49:30
4
lan_kook_7
Mikael_Son :
2026-08-03 13:36:51
9
philipisreal152
Philip Isreal :
howwwww
2026-08-05 19:32:49
0
hydx.aep
hydx.aep :
Yo sunfyre is back😁
2026-08-03 16:20:49
6
zedrix.2k
zedrix :
The half part of their face are also burnt 😭 Sunfyre came back from the dead for him ✋🗿🤚
2026-08-04 08:15:50
3
fer.linesilva
Aline 🦅 :
Usurpador mostrando que meritocracia nunca funcionou nem em série e que a família mesmo existindo um acordo de quem faleceu perante a herança, a família vai brigar e no final não tem justiça nenhuma, nada justo pra ninguém.
2026-08-03 19:22:10
0
kingbee098
bee☆ :
essa cena arrepiou até a alma,slk o sunfyre brotando de volta 🔥
2026-08-03 20:22:47
3
To see more videos from user @fluxo.aep1, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

በጾመ ፍልሰታ ወቅት የምእመናን ቅድመ ዝግጅት ምን መምሰል አለበት ? ፍልሰታ ምን ማለት ነው? ዘወትር ማክሰኞ ፦ትምህርተ ወንጌል ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ለዚህ ጥያቄ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተዋል፤ ‹‹ፍልሰታ ማለት ‹ፈለሰ – ተሰደደ› ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ ✝️ ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበት (የተነሣችበት) ቀን ማለት ነው፡፡ ✝️ ወይም ደግሞ ከሥጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊው ዓለም የተሸጋገረችበት ማለት ነው፡፡›› የጾም ትርጕም ‹‹ጾም›› ማለት ‹‹ጾመ –  ተወ፤ ታቀበ፤ ታረመ፤›› ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ቃል ሲኾን የቃሉ ትርጕም ደግሞ ምግብ መተው፣ መከልከልና መጠበቅ ማለት ነው ሲሉ ዲያቆን ቃኘው ወልዴ በ፲፱፻፺፭ ዓ.ም ባዘጋጁት ‹‹ጾምና ምጽዋት›› በሚለው መጽሐፋቸው ገጽ ፰ ላይ ገልጸውታል፡፡ ✝️ የኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላትም የሚያትተውም ይህንኑ ሐሳብ ነው፡፡  ✝️ ጾም ጥሉላትን፣ መባልዕትን ፈጽሞ መተው፣ ሰውነትን ከመብልና ከመጠጥ እንደዚሁም ከሌላውም ክፉ ነገር ዅሉ መጠበቅ፣ መግዛት፣ መቈጣጠር፣ በንስሐ ታጥቦ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር መቅረብና እርሱንም ደጅ መጥናት ማለት ነው፡፡  ✝️ ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ካሣ እና ቀሲስ ስንታየሁ አባተ የሚሰጡት ማብራርያም ይህንኑ ትርጕም የሚያጠናክር ነው፡፡ የጾም ሥርዓቱና ጥቅሙ  ✝️‹‹መላው ሕዋሳታችን ካልጾሙ የምግብና መጠጥ ጾም ብቻ ዋጋ የለውም፡፡ መጽሐፉም የሚለው ‹ወደ አፍ የሚገባ ሰውን አያረክስም፤ ከአፍ የሚወጣ እንጂ› ነው ስለዚህ ዐይን፣ ጆሮ፣ እግርና እጅ የመሳሰሉት የስሜት ሕዋሳታችን መጾም አለባቸው፡፡ ✝️ ከምግብና መጠጥ ይልቅ የሚበልጡት እነዚህ ናቸው፡፡ ከምግብና መጠጥ የምንቆጠበው በራሱ ኃጢአት ስለ ኾነ ሳይኾን ምግብና መጠጥ ሥጋን አጥግቦ በገደል ስለሚጥል ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ስለሚጎትት ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት እንዲቋረጥ ይደረጋል፡፡ ✝️ ስንጾምም ከሐሜት፣ ከአሉባልታ፣ ከዝሙትና በሐሰት ከመመስከር፣ ወዘተ. መቆጠብ አለብን›› ሲሉ ሊቀ ማእምራን ደጉ ያስረዳሉ፡፡ ✝️‹‹የጾም መሠረቱ ሃይማኖት ነው፡፡ በሃይማኖት የተነሣ ለተወሰኑ ጊዜያት ከምግብና ከመጠጥ የምንከለከልበት ኹኔታ ይኖራል፡፡ ነገር ግን ጾም ይህ ብቻ አይደለም፤ ሁለት ዓይነት መስመር አለው፡፡ ✝️  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአጽዋማት ወቅት ከምግበ ሥጋና ከኃጢአት ትከለክላለች፡፡ ከኃጢአት ዅልጊዜም እንከላከላለን፡፡ ከምግብ የምንከለከለው ምግብ ኃጢአት ስለኾነ ሳይኾን ከሃይማኖት የተነሣ ነው፡፡  ✝️ምግብ በልተን ፈቃደ ሥጋችንን ከምናደልብ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋችንን ጎስመን ያለ ምግብና ያለ መጠጥ እግዚአብሔርን እያመሰገንን የምንኖርበትን ሰማያዊና ዘለዓለማዊ ሕይወት የምናስብብት መንገድ ነው››  የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? ✝️የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? ለሚለው ጥያቄ ሊቀ ማእምራን ደጉ ምላሽ ሲሰጡም ‹‹ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐሥራት አገር በመኾኗ እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ስላላቸው መሬት ላይ እየተኙ፣ ጥሬ እየበሉ በሰላም በፍቅር ይጾሙታል፡፡ ✝️ ምእመናን ፍልሰታን ከሌሎች አጽዋማት በተለየ መልኩ መሬት ላይ እየተኙ ይጾሙታል፡፡ ✝️ ይህ ደግሞ የእመቤታችን ፍቅር ስለሳባቸው ነው፤››፡፡ ✝️ ኢትዮጵያውያንም ለእመቤታችን ያላቸው ፍቅር የተለየ ነው፡፡ ይህም ከእመቤታችን ጋር ያለንን የጠበቀ ትስስር የሚያመላክት ሲኾን ከዚህም ሌላ አገራችን ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐሥራት አገር ናት፡፡ ✝️ እመቤታችን ልጇ ወዳጇ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስን ይዛ በተሰደደችበት ወቅት በግብጽ ብቻ ሳይኾን በኢትዮጵያ ምድርም መጥታ ዐርፋለች፡፡  ✝️ በዚህ ጊዜ አራቱንም የአገሪቱን መዓዝን ባርካለች፡፡ ሊቃውንቱ እንደሚያስተምሩት ነቢዩ ዕንባቆም ‹‹የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ›› በማለት የተናገረው ትንቢትም እመቤታችን ልጇን ይዛ ወደ ኢትዮጵያ መምጣቷን ያጠይቃል፡፡ ስለዚህ ይህን ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ሥርዓት አድርገን ፍልሰታን በልዩ ኹኔታ እንጾማለን፡፡ ✝️ ድርሳነ ዑራኤልም ‹‹እመቤታችን ድንግል ማርያም በስደቷ ወራት ልጇ ሕፃኑ ኢየሱስን ይዛ ከምድረ እስራኤል ወደ ምድረ ግብጽ፣ ከዚያም ወደ ብሔረ ኢትዮጵያ መጥታ በቅዱስ ዑራኤል መሪነት በደብረ ዳሞ፣ በትግራይ፣ በጎንደር፣ በአክሱም፣ በደብር ዐባይ፣ በጐጃምና በጣና በአደረገችው የስደት ጉዞ ሕፃኑ ኢየሱስ ለድንግል እናቱ ‹ኢትዮጵያን ዐሥራት አድርጌ ሰጥቼሻለሁ››› በማለት በሸዋና በወሎ፣ በሐረርጌና በአርሲ፣ በሲዳማና በባሌ፣ በከፋና በኢሉባቦር፣ በወለጋና በሌሎችም የኢትዮጵያ ክፍላተ አህጉር በብሩህ ደመና ተጭነው በአየር እየተዘዋወሩ ተራራውንና ወንዙን (አፍላጋቱን) እንደ ጐበኙ ይናገራል፡፡ በጾመ ፍልሰታ ወቅት የምእመናን ቅድመ ዝግጅት ✝️በጾመ ፍልሰታ ወቅት ምእመናን ምን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አለባቸው? ሱባዔ ከገቡ በኋላስ ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል? የሚለውም ሌላው ጥያቄአችን ነበር፡፡  ✝️ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም እንዲህ ይመልሳሉ፤ ‹‹ምእመናን ጾም (ሱባዔ) ከመጀመራቸው በፊት የሥጋን ኮተት ዅሉ ማስወገድ አለባቸው፡፡ ሐሳባቸው ዅሉ ወደተለያየ አቅጣጫ ሳይከፋፈል ልቡናቸውን ሰብስበው ለአንድ እምነት መቆም፣ ከሱባዔ የሚያቋርጣቸውን ጉዳይም አስቀድሞ ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል፡፡ ✝️ ከገቡ በኋላም ሥጋቸውን ማድከም፣ በጾም በጸሎት መጠመድ አለባቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር እንደ ተሰጣቸው ጸጋ መጠን ቤተ ክርስቲያንን ማገልገል ይገባቸዋል፡፡ ✝️ ጉልበት ያለው በጉልበቱ፣ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ ዕውቀት ያለው በዕውቀቱ፣ አቅሙ የደከመን መርዳት የማይችል ደግሞ ምክርና ሐሳብ በመስጠት ክርስቲያናዊ ድርሻውን ይወጣ፡፡ ✝️ ብዙ ከመብላት ጥቂት በመመገብ፣ ብዙ የሚያሰክር መጠጥ ጠጥቶ ከመንገዳገድ ውኃን ብቻ በመጎንጨት ለቁመተ ሥጋ የሚያበቃቸውን ያህል እያደረጉ ፈጣሪያቸውን ይጠይቁ፡፡ አለባበስን በተመለከተም ሥርዓት ያለው አለባበስ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ከሌላው የተለየና የሌሎችን ቀልብ የሚስብ  ልብስ መኾን የለበትም፡፡›› ቀሲስ ስንታየሁ የተናገሩትም ከሊቀ ማእምራን ደጉ ትምህርት ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡  ✝️‹‹ጾም ማለት ለእግዚአብሔር ማመልከቻ ማስገባት ማለት ነው፡፡ የነነዌ ሰዎች ሦስት ቀን ጾሙ፤ በሦስት ቀናት ውስጥ አገራቸው ከመከራ ዳነች፡፡ የፍልሰታ  ✝️ጾምም ‹የወገኖቻችንን፣ በአጠቃላይ የሰውን ልጅ ጥፋት አታሳየን› ብለን ቦታና ጊዜ ወስነን ሱባዔ የምንይዝበት ጾም ነው፡፡ እኛ ምእመናን ከሁለት መቶ ኀምሳ ቀናት በላይ እንጾማለን፡፡ ነገር ግን ስንጾም ማየት የሚገባን ነገር አለ፡፡ ‹ፍቅር እንደ ሸማ ያላብስህ› እንደሚባለው ስንጾም ፍቅር ሊኖረን ይገባል፡፡ ጾም ያለ ፍቅር፣ ፍቅርም ያለ ጾም ዋጋ የለውም፡፡ ቁም ነገሩ እኛ በጾም ደርቆ መዋል ሳይኾን ፍቅርና ሰላም መታከል አለበት፡፡ የተጣላ መታረቅ አለበት፡፡ ✝️ በቅዳሴ ሰዓት ቦታ ላጡ ቦታ መስጠት፣ አቅመ ደካሞችን መርዳት፣ በተለይ አረጋውያንንና ሕፃናትን መደገፍ የወጣቶች ድርሻ ነው፡፡ በቅዳሴ ሰዓት የበረታው ለደከመው ቦታ መልቀቅ ይኖርበታል፡፡ በቤተ ክር
በጾመ ፍልሰታ ወቅት የምእመናን ቅድመ ዝግጅት ምን መምሰል አለበት ? ፍልሰታ ምን ማለት ነው? ዘወትር ማክሰኞ ፦ትምህርተ ወንጌል ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ለዚህ ጥያቄ የሚከተለውን ምላሽ ሰጥተዋል፤ ‹‹ፍልሰታ ማለት ‹ፈለሰ – ተሰደደ› ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ ✝️ ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበት (የተነሣችበት) ቀን ማለት ነው፡፡ ✝️ ወይም ደግሞ ከሥጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊው ዓለም የተሸጋገረችበት ማለት ነው፡፡›› የጾም ትርጕም ‹‹ጾም›› ማለት ‹‹ጾመ – ተወ፤ ታቀበ፤ ታረመ፤›› ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ቃል ሲኾን የቃሉ ትርጕም ደግሞ ምግብ መተው፣ መከልከልና መጠበቅ ማለት ነው ሲሉ ዲያቆን ቃኘው ወልዴ በ፲፱፻፺፭ ዓ.ም ባዘጋጁት ‹‹ጾምና ምጽዋት›› በሚለው መጽሐፋቸው ገጽ ፰ ላይ ገልጸውታል፡፡ ✝️ የኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላትም የሚያትተውም ይህንኑ ሐሳብ ነው፡፡ ✝️ ጾም ጥሉላትን፣ መባልዕትን ፈጽሞ መተው፣ ሰውነትን ከመብልና ከመጠጥ እንደዚሁም ከሌላውም ክፉ ነገር ዅሉ መጠበቅ፣ መግዛት፣ መቈጣጠር፣ በንስሐ ታጥቦ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር መቅረብና እርሱንም ደጅ መጥናት ማለት ነው፡፡ ✝️ ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም ካሣ እና ቀሲስ ስንታየሁ አባተ የሚሰጡት ማብራርያም ይህንኑ ትርጕም የሚያጠናክር ነው፡፡ የጾም ሥርዓቱና ጥቅሙ ✝️‹‹መላው ሕዋሳታችን ካልጾሙ የምግብና መጠጥ ጾም ብቻ ዋጋ የለውም፡፡ መጽሐፉም የሚለው ‹ወደ አፍ የሚገባ ሰውን አያረክስም፤ ከአፍ የሚወጣ እንጂ› ነው ስለዚህ ዐይን፣ ጆሮ፣ እግርና እጅ የመሳሰሉት የስሜት ሕዋሳታችን መጾም አለባቸው፡፡ ✝️ ከምግብና መጠጥ ይልቅ የሚበልጡት እነዚህ ናቸው፡፡ ከምግብና መጠጥ የምንቆጠበው በራሱ ኃጢአት ስለ ኾነ ሳይኾን ምግብና መጠጥ ሥጋን አጥግቦ በገደል ስለሚጥል ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ስለሚጎትት ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ግንኙነት እንዲቋረጥ ይደረጋል፡፡ ✝️ ስንጾምም ከሐሜት፣ ከአሉባልታ፣ ከዝሙትና በሐሰት ከመመስከር፣ ወዘተ. መቆጠብ አለብን›› ሲሉ ሊቀ ማእምራን ደጉ ያስረዳሉ፡፡ ✝️‹‹የጾም መሠረቱ ሃይማኖት ነው፡፡ በሃይማኖት የተነሣ ለተወሰኑ ጊዜያት ከምግብና ከመጠጥ የምንከለከልበት ኹኔታ ይኖራል፡፡ ነገር ግን ጾም ይህ ብቻ አይደለም፤ ሁለት ዓይነት መስመር አለው፡፡ ✝️ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአጽዋማት ወቅት ከምግበ ሥጋና ከኃጢአት ትከለክላለች፡፡ ከኃጢአት ዅልጊዜም እንከላከላለን፡፡ ከምግብ የምንከለከለው ምግብ ኃጢአት ስለኾነ ሳይኾን ከሃይማኖት የተነሣ ነው፡፡ ✝️ምግብ በልተን ፈቃደ ሥጋችንን ከምናደልብ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋችንን ጎስመን ያለ ምግብና ያለ መጠጥ እግዚአብሔርን እያመሰገንን የምንኖርበትን ሰማያዊና ዘለዓለማዊ ሕይወት የምናስብብት መንገድ ነው›› የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? ✝️የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? ለሚለው ጥያቄ ሊቀ ማእምራን ደጉ ምላሽ ሲሰጡም ‹‹ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐሥራት አገር በመኾኗ እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ስላላቸው መሬት ላይ እየተኙ፣ ጥሬ እየበሉ በሰላም በፍቅር ይጾሙታል፡፡ ✝️ ምእመናን ፍልሰታን ከሌሎች አጽዋማት በተለየ መልኩ መሬት ላይ እየተኙ ይጾሙታል፡፡ ✝️ ይህ ደግሞ የእመቤታችን ፍቅር ስለሳባቸው ነው፤››፡፡ ✝️ ኢትዮጵያውያንም ለእመቤታችን ያላቸው ፍቅር የተለየ ነው፡፡ ይህም ከእመቤታችን ጋር ያለንን የጠበቀ ትስስር የሚያመላክት ሲኾን ከዚህም ሌላ አገራችን ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐሥራት አገር ናት፡፡ ✝️ እመቤታችን ልጇ ወዳጇ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስን ይዛ በተሰደደችበት ወቅት በግብጽ ብቻ ሳይኾን በኢትዮጵያ ምድርም መጥታ ዐርፋለች፡፡ ✝️ በዚህ ጊዜ አራቱንም የአገሪቱን መዓዝን ባርካለች፡፡ ሊቃውንቱ እንደሚያስተምሩት ነቢዩ ዕንባቆም ‹‹የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ›› በማለት የተናገረው ትንቢትም እመቤታችን ልጇን ይዛ ወደ ኢትዮጵያ መምጣቷን ያጠይቃል፡፡ ስለዚህ ይህን ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ሥርዓት አድርገን ፍልሰታን በልዩ ኹኔታ እንጾማለን፡፡ ✝️ ድርሳነ ዑራኤልም ‹‹እመቤታችን ድንግል ማርያም በስደቷ ወራት ልጇ ሕፃኑ ኢየሱስን ይዛ ከምድረ እስራኤል ወደ ምድረ ግብጽ፣ ከዚያም ወደ ብሔረ ኢትዮጵያ መጥታ በቅዱስ ዑራኤል መሪነት በደብረ ዳሞ፣ በትግራይ፣ በጎንደር፣ በአክሱም፣ በደብር ዐባይ፣ በጐጃምና በጣና በአደረገችው የስደት ጉዞ ሕፃኑ ኢየሱስ ለድንግል እናቱ ‹ኢትዮጵያን ዐሥራት አድርጌ ሰጥቼሻለሁ››› በማለት በሸዋና በወሎ፣ በሐረርጌና በአርሲ፣ በሲዳማና በባሌ፣ በከፋና በኢሉባቦር፣ በወለጋና በሌሎችም የኢትዮጵያ ክፍላተ አህጉር በብሩህ ደመና ተጭነው በአየር እየተዘዋወሩ ተራራውንና ወንዙን (አፍላጋቱን) እንደ ጐበኙ ይናገራል፡፡ በጾመ ፍልሰታ ወቅት የምእመናን ቅድመ ዝግጅት ✝️በጾመ ፍልሰታ ወቅት ምእመናን ምን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አለባቸው? ሱባዔ ከገቡ በኋላስ ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል? የሚለውም ሌላው ጥያቄአችን ነበር፡፡ ✝️ሊቀ ማእምራን ደጉ ዓለም እንዲህ ይመልሳሉ፤ ‹‹ምእመናን ጾም (ሱባዔ) ከመጀመራቸው በፊት የሥጋን ኮተት ዅሉ ማስወገድ አለባቸው፡፡ ሐሳባቸው ዅሉ ወደተለያየ አቅጣጫ ሳይከፋፈል ልቡናቸውን ሰብስበው ለአንድ እምነት መቆም፣ ከሱባዔ የሚያቋርጣቸውን ጉዳይም አስቀድሞ ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል፡፡ ✝️ ከገቡ በኋላም ሥጋቸውን ማድከም፣ በጾም በጸሎት መጠመድ አለባቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር እንደ ተሰጣቸው ጸጋ መጠን ቤተ ክርስቲያንን ማገልገል ይገባቸዋል፡፡ ✝️ ጉልበት ያለው በጉልበቱ፣ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ ዕውቀት ያለው በዕውቀቱ፣ አቅሙ የደከመን መርዳት የማይችል ደግሞ ምክርና ሐሳብ በመስጠት ክርስቲያናዊ ድርሻውን ይወጣ፡፡ ✝️ ብዙ ከመብላት ጥቂት በመመገብ፣ ብዙ የሚያሰክር መጠጥ ጠጥቶ ከመንገዳገድ ውኃን ብቻ በመጎንጨት ለቁመተ ሥጋ የሚያበቃቸውን ያህል እያደረጉ ፈጣሪያቸውን ይጠይቁ፡፡ አለባበስን በተመለከተም ሥርዓት ያለው አለባበስ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ከሌላው የተለየና የሌሎችን ቀልብ የሚስብ ልብስ መኾን የለበትም፡፡›› ቀሲስ ስንታየሁ የተናገሩትም ከሊቀ ማእምራን ደጉ ትምህርት ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ ✝️‹‹ጾም ማለት ለእግዚአብሔር ማመልከቻ ማስገባት ማለት ነው፡፡ የነነዌ ሰዎች ሦስት ቀን ጾሙ፤ በሦስት ቀናት ውስጥ አገራቸው ከመከራ ዳነች፡፡ የፍልሰታ ✝️ጾምም ‹የወገኖቻችንን፣ በአጠቃላይ የሰውን ልጅ ጥፋት አታሳየን› ብለን ቦታና ጊዜ ወስነን ሱባዔ የምንይዝበት ጾም ነው፡፡ እኛ ምእመናን ከሁለት መቶ ኀምሳ ቀናት በላይ እንጾማለን፡፡ ነገር ግን ስንጾም ማየት የሚገባን ነገር አለ፡፡ ‹ፍቅር እንደ ሸማ ያላብስህ› እንደሚባለው ስንጾም ፍቅር ሊኖረን ይገባል፡፡ ጾም ያለ ፍቅር፣ ፍቅርም ያለ ጾም ዋጋ የለውም፡፡ ቁም ነገሩ እኛ በጾም ደርቆ መዋል ሳይኾን ፍቅርና ሰላም መታከል አለበት፡፡ የተጣላ መታረቅ አለበት፡፡ ✝️ በቅዳሴ ሰዓት ቦታ ላጡ ቦታ መስጠት፣ አቅመ ደካሞችን መርዳት፣ በተለይ አረጋውያንንና ሕፃናትን መደገፍ የወጣቶች ድርሻ ነው፡፡ በቅዳሴ ሰዓት የበረታው ለደከመው ቦታ መልቀቅ ይኖርበታል፡፡ በቤተ ክር

About