@behajanews: የመንግስት ጥብቅ የተፈጥሮ ደን ዛፍ ቆርጠው ተሸክመው ሲሄዱ እጅ ከፍንጅ የተያዙ አካላት በእስራትና በገንዘብ ተቀጡ አርባምንጭ ፣ነሐሴ 13/2018 ዓ፣ም(አርባ ምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን) የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት በአርባምንጭ ከተማ በመንግስት ይዞታ ጥብቅ የተፈጥሮ ደን ውስጥ የደን ዛፍ ቆርጠው ተሸክመው ሲሄዱ እጅ ከፍንጅ የተያዙ አካላት ላይ የእስራትና የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል። የአርባምንጭ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተከሳሾች የኢ.ፌ.ድ.ሪ.ወ.ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና የደን ልማት ጥበቃ እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1065/2010 አንቀጽ 25(4) (ሀ) እና (ሠ ) 26(1) የተደነገገዉን በመተላለፋቸው አንድ ዓመት ከስድስት ወር እስራት እና በ10,000 ( አስር ሺ ) ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል ። ተከሳሾች በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በቀን ዐ8/12/2018 ዓ/ም በግምት ከምሽቱ 1፡30 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ያለፈቃድ በህገወጥ መንገድ ወደ አርባምንጭ ጥብቅ ደን ውስጥ በመግባት ተጠብቆና ተከልሎ ካለው ደን የማገዶ እንጨት በመቁረጥ እያንዳንዳቸው አንዳንድ ሸክም በድምሩ 12 ሸክም በጀርባቸው እንደተሸከሙ እጅ ፍንጅ በመያዛቸው በፈጸሙት የደን ውጤት የሆነውን እንጨት ይዞ በመገኘት ወንጀል ተከሰዋል። ወንጀሉን የፈጸሙት ግለሰቦቹ 1ኛ አልማዝ ድርሳ፣ 2ኛ/ ማርታ ማዣ፣3ኛ ዓይናለም ባቤና፣ 4ኛ/ ገነት አባ ፣5ኛ/ ገነት ኡፎ ፣ 6ኛ/ መቅደስ ጠጆ፣ 7ኛ/ ዓለም አበበ ፣ 8ኛ/ ኩንታሬ ኩካ ፣ 9ኛ/ ሴጌቴ ሳቦ ፣ 10ኛ/ አማረች ዝዳ ፣ 11ኛ/ ትዕግስት ሹርካ እና 12ኛ/ አንዷለም አብይ እንደሆኑ የክሱ መዝገብ ያሳያል። የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ውሳኔው የኢ.ፌ.ድ.ሪ.ወ.ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና የደን ልማት ጥበቃ እና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1065/2010 አንቀጽ 25(4) ሠ) እና 26(1) የተደነገገዉን ድንጋጌ በመተላለፍ የቀረበ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ሌሎችን ከመሰል የወንጀል ድርጊቶች ለማስተማር የተላለፈ ውሳኔ እንደሆነም አመላክቷል። የአርባምንጭ ከተማ ፍትህ መምሪያ በበኩሉ ውሳኔው በተደጋጋሚ እየተፈፀመ የሚገኘውን ወንጀል ለማስቆም ፈጣንና ፍትሃዊ መሆኑን ገልፆ በተለይም የበርካታ ብዝኃ ሕይወት መገኛና ውድ ሥነ-ምህዳርን በታቀፈው ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክና የአርባምንጭ የተፈጥሮ ደን ላይ የሚደርስ ጉዳትን ለማስቀረት የሚያግዝ እንደሆነም አስታውቋል። በአሰፋ ጪሻ #behajanews #ethiopiannews #እናቶች #ችግኝ #አርባምንጭ
BEHAJA NEWS
Region: ET
Thursday 20 August 2026 04:24:35 GMT
Music
Download
Comments
ኢዮራም :
ህግ ድሀ ላይ የሚበረታው ለምንድን ነው
2026-08-20 07:34:27
141
abdurehim56 :
ከቲባው ይታሰርልን
2026-08-20 04:38:57
172
miko bezabih21 27 :
yemote hager west new yenew
2026-08-20 05:10:21
0
Raya :
የፈረሰ መግስት
2026-08-20 04:31:17
146
ናታኔም&አምነን :
are tewun begeta sew yenurebet
2026-08-20 10:15:21
0
habtìsh :
ሀንግ የሰራው በ3ወር ሲፈታ እናቶችን 1አመት ከ 6 ወር
2026-08-20 07:06:26
58
ብርሀኑ :
የክልሉ መንግስት እራሱ መታሰር አለበት
2026-08-20 07:47:47
18
Geez🇪🇹🇪🇹🇪🇹 :
asafary!!!
2026-08-20 08:13:20
1
Gashu :
😭😭😭😭😭😭😭😭😭 yet ager new
2026-08-20 09:41:59
0
siab :
እንደው እንደ ብልፅግና አይነት ጉድ እርግማን ነው
2026-08-20 05:21:50
21
Rohobot Media :
1 አመት🙄🙄ይሁን 10,000 ይሄ ቢኖር ይሸከሙ ነበር 🤔🤔🤔
2026-08-20 05:59:38
5
@Mustafi :
አይ ሀገሬ ድሆች እንዳይበሉ ሚከለከልባት ሀገር 😥😥😥😥😥
2026-08-20 04:34:28
32
lôlĩťâ :
መንግስት ድህነትን ሳይሆን ድሀን ለማትፋት ቆርጦ ተነስቷል
2026-08-20 10:37:26
16
nuru seid :
ጉድ በል ጎንዴር ኑሮአቸው እንደመቀየር እስር እና ገንዘብ ቅጣት
2026-08-20 05:47:04
15
dawit :
eeeeee
2026-08-20 08:50:35
0
josh :
ከአውሬ ለይቼ ማላየው መንግስት
2026-08-20 05:33:11
13
mame :
እናቶች ናቸው መታሰር የለባቸውም
2026-08-20 04:37:08
16
አባዝምታ :
ኡኡኡኡኡኡኡ እረ ይሄን መንግስት አንድ እንበለው ጎበዝ
2026-08-20 04:33:24
8
zinash :
እናት ባትራብ እጨት አትለቅምም አይ እናት ሀገሬ ያሳዝናል
2026-08-20 05:24:30
5
1 SOl :
ህግ ድሀ ላይ ነው የሚሰራው 😏
2026-08-20 09:36:16
2
Arsenal / win :
ere mengist tew
2026-08-20 07:56:00
3
dicor ዲኮር ferhan :
መቼስ እርጥብ አይቆርጡ .. ለማገዶ .. የደረቀ ጭራሮ የረገፈ ቅጠል ጠርገው ኑሮን በታገሉ...😭😭😭😭
2026-08-20 14:30:33
1
YirgaNafu@4321 :
አይ ሀገር
2026-08-20 06:17:21
2
jorga :
ምን ማለት ነው አልገባኝም ቀልድ ነወ በለኝ
2026-08-20 07:35:08
3
natanem :
አይ አገሬ ያሳዝናል
2026-08-20 04:34:11
5
To see more videos from user @behajanews, please go to the Tikwm
homepage.