@mzijo5: اهم مابه بياض الوجه والسمعه . #tiktok#fyp

المزن ّ .
المزن ّ .
Open In TikTok:
Region: SA
Friday 21 August 2026 12:14:08 GMT
22756
1396
18
221

Music

Download

Comments

abwmohammad416
ابو محمد🇾🇪♥🌴 :
حي عينك ياذيب 👏👏👏👏
2026-08-21 18:54:11
0
sss____711
مششعل🐆. :
حلوااااا👏👏
2026-08-21 17:10:24
0
9pi0_
سعيد | 𝐀𝐥 𝐐𝐚𝐡𝐭𝐚𝐧𝐢 :
يسّلاااام ❤️
2026-08-21 18:49:07
0
user3094180558439
سنافي 711 :
الله اشهد انه قال
2026-08-21 18:23:24
0
w_7s04
ذأتٌ :
يسلام 👏🏻
2026-08-21 12:55:10
1
b.n.r..1
ᴀʙᴜ ᴏʙᴀɪᴅ ♪ :
ياسلامم❣️.
2026-08-21 16:23:57
0
w9_du
𝐰𝟗ّ . :
ياسَسلاام👏🏻.
2026-08-21 16:49:33
0
r.esc1
𝐺𝐻𝐴𝑅𝐼𝐵 ✨ :
الله الله 👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏
2026-08-21 15:16:41
0
eishq.8
عشق بن مانع 🩶 :
عناد ذا الحساب يصلح لك تصميم @aind.911
2026-08-21 12:31:56
1
user6923516137042
الوهيبي بنيه الرشيدي :
😁😁😁
2026-08-21 16:56:47
0
To see more videos from user @mzijo5, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

የማርያም እርገት (ፍልሰታ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 16 ቀን የሚጾመውን የጾመ ፍልሰታ ሱባኤ ተከትሎ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ወደ ሰማይ ማረጉ የሚዘከርበት ታላቅና ቅዱስ በዓል ነው።
የማርያም እርገት (ፍልሰታ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 16 ቀን የሚጾመውን የጾመ ፍልሰታ ሱባኤ ተከትሎ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ወደ ሰማይ ማረጉ የሚዘከርበት ታላቅና ቅዱስ በዓል ነው። "ፍልሰታ" ማለት ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መፍለስ ወይም መሻገር ማለት ሲሆን፣ እመቤታችን ከምድር ወደ ሰማይ መውጣቷን ያመለክታል።  ✍️✍️✍️✍️ የእርገቷ ታሪክ የሚከተሉትን ዋና ዋና ሁነቶች ይዟል፡✍️✍️ ✍️የዕረፍትና የትንሣኤ ታሪክ የእመቤታችን ዕረፍት (ጥር 21)፦ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ላይ 64 ዓመታት ከኖረች በኋላ በጥር 21 ቀን አረፈች። ሐዋርያት ሥጋዋን ሊቀብሩ ወደ ጌተሰማኒ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ በቅናት ተነሳስተው ሥጋዋን ለማቃጠል ሞከሩ። በዚህ ጊዜ ታውፋንያ የተባለው አይሁዳዊ የአልጋዋን ጠርዝ ሲይዝ መልአከ እግዚአብሔር እጆቹን ቀጣቸው። ወደ ገነት መወሰድ፦ እግዚአብሔር የእናቱን ሥጋ ከአይሁድ እጅ ጠብቆ በደመና ነጥቆ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር እንዲቀመጥ አደረገ። ወንጌላዊው ዮሐንስም ይህንን ምሥጢር በመንፈስ ቅዱስ ተነጥቆ አየ።  ✍️የሐዋርያት ጾምና የትንሣኤዋ መገለጥ ✍️የመጀመሪያው ሱባኤ፦ ዮሐንስ ያየውን ምሥጢር ለሌሎቹ ሐዋርያት ሲነግራቸው "ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ" በማለት ሥጋዋን ያዩ ዘንድ በነሐሴ መጀመሪያ ላይ ጾምና ጸሎት (ሱባኤ) ያዙ። በ15ኛው ቀን (ነሐሴ 14) መላእክት ሥጋዋን አምጥተው ሰጧቸውና በክብር ቀበሯት።  ✍️በትንሣኤ መነሣት (ነሐሴ 16)፦ ከተቀበረችበት ከሦስተኛው ቀን በኋላ (በነሐሴ 16) እንደ ልጇ ትንሣኤ ተነሥታ ወደ ሰማይ ዐረገች።  ✍️የቅዱስ ቶማስ ምስክርነት፦ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ሲመለስ እመቤታችን ስታርግ አየር ላይ አገኛት። እርሷም ትንሣኤዋን እንዲያምን የተገነዘበችበትን ሰበን (መግነዝ) ሰጠችው። ቶማስ ወደ ሐዋርያት መጥቶ እንዳልሰማ ሆኖ "ሥጋዋ የታለ?" አላቸው። መቃብሯን ሲከፍቱ ባዶ ሆኖ አገኙት፤ ከዚያም ቶማስ የሆነውን ሁሉ ነግሯቸው የሰጠችውን ሰበን አካፈላቸው (ዛሬም ካህናት በእጃቸው የሚይዙት መሶበ ወርቅ ወይም ሰበን የዚህ ምልክት ነው)።  ✍️የሁለተኛው ዓመት ጾም፦ በምቀናው ዓመት ሐዋርያት ቶማስ ያየውን ትንሣኤና ዕርገት እኛም በዓይናችን እንይ ብለው ከነሐሴ 1 ጀምረው እንደገና ጾሙ። በነሐሴ 16 ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱን ይዞ መጣ፤ ራሱ ቀዳሽ፣ ጴጥሮስ ረዳት ካህን፣ እስጢፋኖስ ዋና ዲያቆን ሆነው ቅዱስ ቁርባን አቀበሏቸውና ትንሣኤዋን አዩ። 

About