@elvabaezyegros: #recuerdos

🔮Eva la paraguayita🇵🇾
🔮Eva la paraguayita🇵🇾
Open In TikTok:
Region: PY
Monday 24 August 2026 15:27:56 GMT
1043
124
1
0

Music

Download

Comments

angelpkf67e
David :
🥰🥰🥰
2026-08-24 15:49:24
0
To see more videos from user @elvabaezyegros, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

መሬማ 🧕🕌 ✍️ብዙዎች ይህን ዜማ በአረብ ሀገራት የሚገኙ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችንን መከራ የሚዘክር አድርገው ተመልክተውታል  ለእኔ ግን ይህ ትርጉም ብቻውን በቂ ሆኖ አላገኘሁትም የቴዲ የጥበብ ስራዎች ሁሌም በሰምና ወርቅ የታሸጉ ከአንድ በላይ የትርጉም በሮች ያላቸው መሆናቸውን ለሚያስተውል ሰው 'መሬማ'የዜግነት ድንበርን ተሻግራ ሌላ ታሪክ ትነግረናለች   ✨ ውድ ቤተሰቦቼ አንድ ብዬ በዝ-ፀዳል የጀመርኩት የቴዲ አዲስ አለሰበም ኩምኮማዬ😁 በማህበራዊ ሚዲያው መድረክ ላይ እጅግ አነጋጋሪ በሆነው እጅግ ውብ በሆነው 'መሬማ' ሙዚቃ 6ኛው ምዕራፍ በበኩሌ የዚህ ታሪክ አካል መሆኔ ብቻ እንዴት እንደሚያስደስተኝ አጠይቁኝ🥰  ታዲያ ወደ ዛሬው ዳሰሳዬ ስመለስ አንድ ጥያቄ በመጠየቅ ልጀምር ለመሆኑ መሬማ' ማነች?  ''እዉነት ኢትዮጵያዊት ስደተኛ ወይስ              የመናዊት አረብ'' 📌ታሪክን የኋሊት ስንበረብር ወደ ኢትዮጵያ የገናነት ዘመን ይወስደናል - የአክሱም ዘመነ መንግስት። ኢትዮጵያዊያን ነገስታት ባብል መንደብ  (Bab El Mendeb chokepoint) ይቆጣጠሩ ደቡብ ዓረብያ ድረስም ያስተዳድሩ ነበር። ሀገረ ናግራን ብዙ የክርስትና ታሪክ የነበረባት የአክሱም ግዛት አካል ነበረች። የአይሁድ ነገስታት በክርስቲያኖች ላይ ያደርሱ የነበረውን ጭቆና እና ግድያ ለማስቆም የአክሱም ነገስታት ህዝባቸውን ለመታደግ ሰፊ ውጊያ እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ያደርጉ ነበር። ከፋርስ (Persia) እና ሃድራሙት ኃይሎች ጋር በተደረጉ ጦርነቶች ሳቢያ የአክሱም ተፅዕኖ በዓረቢያ ላይ ቀነሰ። ከእስልምና መምጣት በኋላ ደግሞ የአክሱም ተፅዕኖና ገናነት በቀይ ባህርና አከባቢው ቀጠና መሸርሸር ጀመረ። የኢኮኖሚ ድቀትንም አስከተለ። በመጨረሻም የአክሱም መንግስት በዮዲት አመጽ ሙሉ ለሙሉ ወደቀ።  ቴዲ በዚህ ሙዚቃው ላይ ይህን ምስጢር በሁለት ረቂቅ መንገዶች ይገልጽልናል በመጀመሪያ ደረጃ መሬማን ሊያናግራት ሲሞክር የምትሰጠው ምላሽ አረብኛውን 'ላ ላ' የሚል ነው  እርግጥ ነው አረብ ሀገር ያሉ ኢትዮጵያዊያንም ይህን ቃል ይጠቀሙታል ነገር ግን ገጣሚው  'ወዲህ አላውቃት'  በማለት የሚጀምረው ስንኝ ልጅቷ ከእሱ ጋር በዜግነትም ሆነ በቀጥታ ማንነት የማትዛመድ የባዕድ ሀገር ዜጋ መሆኗን ፍንጭ ይሰጠናል ​በሌላ በኩል ቴዲ በሊባኖስ በኳታርና በባህሬን ያሉትን ስደተኞች እህት ወንድሜ በማለት ሲጠቅስ መሬማን ግን ባያት አምሳያዬን ይላታል ይህ አገላለጽ እጅግ ጥልቅ የሆነ የሰምና ወርቅ ምስጢር የያዘ ነው ኢትዮጵያና የመን በቀይ ባህር የተከለሉ ቢሆኑም በታሪክ ግን አንዱ የአንዱ ግዛት አካል የነበሩ በደም የተሳሰሩ ህዝቦች ናቸው መሬማን የአያቴ አምሳያ ማለቱ ዜግነቷ የመናዊት ቢሆንም በቀደመው ማንነቷ ግን የጥንት ዘመዱና የወገኑ ደም ያለባት መሆኗን ለማሳየት ነው ​በዜማ ስሜቱን የሚገልፀዉ ገፀባህሪ እራሱን የሚገልጽበት መንገድም  📌ሌላው ማሳያ ነው 'እንዳፋር አፍሌታ የጠየመው ፊቴ' በማለት የአፋርን ጠይምነትና መልክ መጥቀሱ ከየመን ጋር ያለውን መልክዓ ምድራዊና ስነ ልቦናዊ ቅርበት ያጎላዋል እይው ማንነቴን የሚለው ጥሪ እኔ እኮ የራቀሽ ባዕድ አይደለሁም በጥንት ታሪክ የታጨን በመልክና በደም የምንመሳሰል ወገንሽ ነኝ የሚል የሩቅ ትውውቅ ድምፅ ነው በመጨረሻም ቴዲ በዜማው ማሳረጊያ ላይ  የመንያ ያ መሬማ እያለ በጥልቅ ስሜትና በእንጉርጉሮ ሲጣራት የመናዊነቷን አረጋግጦ ይነግረናል እሱ በየመን ጎዳናዎች ላይ የሚያልፍ ጠይም ኢትዮጵያዊ ሲሆን በጉዞው ለቅጽበት የተመለከታትና ቁዘማዋ ያሳዘነው መሬማ ግን የአያቱ ልጅ የሆነችው የመናዊቷ እንስት ነች ​ስለዚህ መሬማ በስደት የሚሰቃዩ እህቶቻችንን መከራ ብቻ ሳይሆን ከድንበር ባለፈ የሰው ልጅን ስቃይ የምታሳይ ጥንታዊ የታሪክ ዝምድናን የምታስታውስና በታሪክ ግንብ የተለዩ ወንድማማች ህዝቦችን የጋራ ህመም የምትዘክር ድንቅ የጥበብ ስራ ነች ብዬ አስባለሁ 📌እስቲ በመጨረሻም ጥቂት ነገር ለጠቅላላ እውቀት ልጨምር እና ለዛሬ ይዤላቹ የመጣሁትን ላብቃ 🙏🥰 💡አፍሌታ፦ አፋር ውስጥ ለውሃ መያዣነት የሚጠቀሙበት፥ ከፍየል ቆዳ የሚሰራ መገልገያ ነው 💡
መሬማ 🧕🕌 ✍️ብዙዎች ይህን ዜማ በአረብ ሀገራት የሚገኙ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችንን መከራ የሚዘክር አድርገው ተመልክተውታል ለእኔ ግን ይህ ትርጉም ብቻውን በቂ ሆኖ አላገኘሁትም የቴዲ የጥበብ ስራዎች ሁሌም በሰምና ወርቅ የታሸጉ ከአንድ በላይ የትርጉም በሮች ያላቸው መሆናቸውን ለሚያስተውል ሰው 'መሬማ'የዜግነት ድንበርን ተሻግራ ሌላ ታሪክ ትነግረናለች ✨ ውድ ቤተሰቦቼ አንድ ብዬ በዝ-ፀዳል የጀመርኩት የቴዲ አዲስ አለሰበም ኩምኮማዬ😁 በማህበራዊ ሚዲያው መድረክ ላይ እጅግ አነጋጋሪ በሆነው እጅግ ውብ በሆነው 'መሬማ' ሙዚቃ 6ኛው ምዕራፍ በበኩሌ የዚህ ታሪክ አካል መሆኔ ብቻ እንዴት እንደሚያስደስተኝ አጠይቁኝ🥰 ታዲያ ወደ ዛሬው ዳሰሳዬ ስመለስ አንድ ጥያቄ በመጠየቅ ልጀምር ለመሆኑ መሬማ' ማነች? ''እዉነት ኢትዮጵያዊት ስደተኛ ወይስ የመናዊት አረብ'' 📌ታሪክን የኋሊት ስንበረብር ወደ ኢትዮጵያ የገናነት ዘመን ይወስደናል - የአክሱም ዘመነ መንግስት። ኢትዮጵያዊያን ነገስታት ባብል መንደብ (Bab El Mendeb chokepoint) ይቆጣጠሩ ደቡብ ዓረብያ ድረስም ያስተዳድሩ ነበር። ሀገረ ናግራን ብዙ የክርስትና ታሪክ የነበረባት የአክሱም ግዛት አካል ነበረች። የአይሁድ ነገስታት በክርስቲያኖች ላይ ያደርሱ የነበረውን ጭቆና እና ግድያ ለማስቆም የአክሱም ነገስታት ህዝባቸውን ለመታደግ ሰፊ ውጊያ እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ያደርጉ ነበር። ከፋርስ (Persia) እና ሃድራሙት ኃይሎች ጋር በተደረጉ ጦርነቶች ሳቢያ የአክሱም ተፅዕኖ በዓረቢያ ላይ ቀነሰ። ከእስልምና መምጣት በኋላ ደግሞ የአክሱም ተፅዕኖና ገናነት በቀይ ባህርና አከባቢው ቀጠና መሸርሸር ጀመረ። የኢኮኖሚ ድቀትንም አስከተለ። በመጨረሻም የአክሱም መንግስት በዮዲት አመጽ ሙሉ ለሙሉ ወደቀ። ቴዲ በዚህ ሙዚቃው ላይ ይህን ምስጢር በሁለት ረቂቅ መንገዶች ይገልጽልናል በመጀመሪያ ደረጃ መሬማን ሊያናግራት ሲሞክር የምትሰጠው ምላሽ አረብኛውን 'ላ ላ' የሚል ነው እርግጥ ነው አረብ ሀገር ያሉ ኢትዮጵያዊያንም ይህን ቃል ይጠቀሙታል ነገር ግን ገጣሚው 'ወዲህ አላውቃት' በማለት የሚጀምረው ስንኝ ልጅቷ ከእሱ ጋር በዜግነትም ሆነ በቀጥታ ማንነት የማትዛመድ የባዕድ ሀገር ዜጋ መሆኗን ፍንጭ ይሰጠናል ​በሌላ በኩል ቴዲ በሊባኖስ በኳታርና በባህሬን ያሉትን ስደተኞች እህት ወንድሜ በማለት ሲጠቅስ መሬማን ግን ባያት አምሳያዬን ይላታል ይህ አገላለጽ እጅግ ጥልቅ የሆነ የሰምና ወርቅ ምስጢር የያዘ ነው ኢትዮጵያና የመን በቀይ ባህር የተከለሉ ቢሆኑም በታሪክ ግን አንዱ የአንዱ ግዛት አካል የነበሩ በደም የተሳሰሩ ህዝቦች ናቸው መሬማን የአያቴ አምሳያ ማለቱ ዜግነቷ የመናዊት ቢሆንም በቀደመው ማንነቷ ግን የጥንት ዘመዱና የወገኑ ደም ያለባት መሆኗን ለማሳየት ነው ​በዜማ ስሜቱን የሚገልፀዉ ገፀባህሪ እራሱን የሚገልጽበት መንገድም 📌ሌላው ማሳያ ነው 'እንዳፋር አፍሌታ የጠየመው ፊቴ' በማለት የአፋርን ጠይምነትና መልክ መጥቀሱ ከየመን ጋር ያለውን መልክዓ ምድራዊና ስነ ልቦናዊ ቅርበት ያጎላዋል እይው ማንነቴን የሚለው ጥሪ እኔ እኮ የራቀሽ ባዕድ አይደለሁም በጥንት ታሪክ የታጨን በመልክና በደም የምንመሳሰል ወገንሽ ነኝ የሚል የሩቅ ትውውቅ ድምፅ ነው በመጨረሻም ቴዲ በዜማው ማሳረጊያ ላይ የመንያ ያ መሬማ እያለ በጥልቅ ስሜትና በእንጉርጉሮ ሲጣራት የመናዊነቷን አረጋግጦ ይነግረናል እሱ በየመን ጎዳናዎች ላይ የሚያልፍ ጠይም ኢትዮጵያዊ ሲሆን በጉዞው ለቅጽበት የተመለከታትና ቁዘማዋ ያሳዘነው መሬማ ግን የአያቱ ልጅ የሆነችው የመናዊቷ እንስት ነች ​ስለዚህ መሬማ በስደት የሚሰቃዩ እህቶቻችንን መከራ ብቻ ሳይሆን ከድንበር ባለፈ የሰው ልጅን ስቃይ የምታሳይ ጥንታዊ የታሪክ ዝምድናን የምታስታውስና በታሪክ ግንብ የተለዩ ወንድማማች ህዝቦችን የጋራ ህመም የምትዘክር ድንቅ የጥበብ ስራ ነች ብዬ አስባለሁ 📌እስቲ በመጨረሻም ጥቂት ነገር ለጠቅላላ እውቀት ልጨምር እና ለዛሬ ይዤላቹ የመጣሁትን ላብቃ 🙏🥰 💡አፍሌታ፦ አፋር ውስጥ ለውሃ መያዣነት የሚጠቀሙበት፥ ከፍየል ቆዳ የሚሰራ መገልገያ ነው 💡"ሙሀማሺን" (ትርጉሙም "የተገለሉ" ማለት ነው) በየመን የሚኖሩ ቁጥራቸው እስከ 3.5 ሚሊዮን የሚደርስ ጥቁር አናሳ ማህበረሰቦች ናቸው። እነዚህ ወገኖች ለዘመናት በዘለቀ የዘር መድልዎ በከፋ ድህነት እና በማህበራዊ መገለል ውስጥ ይገኛሉ። ስለ አመጣጣቸው የተለያዩ መላምቶች ቢኖሩም አብዛኛው የታሪክ ድርሳናት እንደሚጠቁሙት ከ6ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየመን የነበሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወይም ከምስራቅ አፍሪካ (ሱዳን እና ኢትዮጵያ) የፈለሱ ባሮች ዝርያዎች ናቸው ተብሎ ይታመናል። አብዛኞቹ እንደ ሰነዓ ባሉ ትልልቅ ከተሞች ዳርቻ በሚገኙ የድህነት መንደሮች (Slums) ውስጥ ተፋፍገው የሚኖሩ ናቸው ከዚህ ድንቅ አልበም ላይ በሌላ ሙዚቃ አሰክንገኝ ሰላም ቆዩልኝ🙏 📌ምንጭ፦ ቶምሰን ሮይተርስ ፋውንዴሽን ኒውስ እና Habtu A nigus 🗣ክብር ለሚገባው ክብር እንሰጣለን🫡 musictube 🇪🇹 #fyp #Ethiopianmusic #musictube369 #ቴዲአፍሮ💚💛❤ #መሬማ

About