@mariedeem2y: ሰበር ዜና የጉድ ሀገር ባህር ደር ። በባህር ዳር ከተማ ሰዎችን በማገት የተሳተፉ የወንጀል ቡድን አባላትና የመንግስት ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ዋሉ። በባህር ዳር ከተማ በሰዎች ላይ እገታ በመፈፀም፣ ገንዘብ በመጠየቅና በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ የወንጀል ቡድን አባላትና ለወንጀሉ መፈፀሚያነት የዋለ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቀ። ተጠርጣሪውቹ ታጋቾቹን አፍነው በመውሰድ ለ11 ቀናት አግተው ያቆዩዋቸው ሲሆን፤ በወቅቱ ታጋቾቹን ለመልቀቅ 3 ሚሊዮን 370 ሺህ ብር ከቤተሰቦቻቸው በመጠየቅና ገንዘቡ ከተከፈላቸው በኋላ እንዲለቀቁ ማድረጋቸውን የምርመራ መረጃው ያመላክታል። የመምሪያው የወንጀል ምርመራ ምክትል መምሪያ አዛዥ ኮማንደር መኳንንት አድማስ እንደገለጹት ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 14 (ኤፍራታ) አካባቢ ነዋሪና ነጋዴ የሆኑ ሶስት ግለሰቦች በራሳቸው ተሽከርካሪ ወደ ስራ ቦታቸው በመሄድ ላይ እያሉ በወቅቱ ማንነታቸው ባልታወቁ አካላት እገታ ተፈፅሞባቸዋል ብለዋል። ተጠርጣሪዎቹ ታጋቾቹን በመንግስት ተሽከርካሪ አፍነው በመውሰድ ለ11 ቀናት አግተው ማቆየታቸውን ያስረዱት ኮማንደር መኳንንት የወንጀሉ አደራጆች እና ተሳታፊዎች በቅንጅት የሰሩ መሆኑን አክለው አስታውቀዋል። በተደረገው ጥብቅ ክትትልም 1ኛ. ወንጀሉን በዋናነት ያስተባበረው አብርሃም ጫኔ የተባለ በቀበሌ 06 የኤሌክትሮኒክስ ሱቅ ባለቤት፤ 2ኛ. ተሽከርካሪን ለወንጀል ያዋለ መለሰ ጌትነት የተባለ አሽከርካሪ ግለሰብ፤ 3ኛ. ታጋቾቹን ደብቆ ያቆየውና ወንጀሉን የሸፈነው በቀበሌ 14 እንዘግድብ አካባቢ የሚገኝ ህንፃ አስተዳዳሪ (170 ሺህ ብር ክፍያ በመቀበል ወንጀሉን ያደባበሰ)፤ 4ኛ. አበበ ጌቴ፣ ከአዲስ አበባ የተሳተፈ ተባባሪን ጨምሮ እስከ 870 ሺህ ብር በባንክ አካውንት ገቢ በማድረግ ረገድ የተሳተፉ አባላት፤ በአጠቃላይ አምስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ኮማንደር መኳንንት ያስታወቁት። በተጨማሪም ለወንጀሉ ማስፈፀሚያነት የዋሉ አንድ ማካሮቭ  እና አንድ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያዎች ከነተሽከርካሪው መያዛቸውን ገልጸዋል። የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንግስት ተቋማት ለስራ የተመደቡላቸውን ተሽከርካሪዎችና አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ሊያደርጉ እንደሚገባ ያሳሰበ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት ቀሪ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለፍርድ ቤት ለማቅረብ የሚያስችል ጥብቅ የምርመራ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።

የባህር ዳሯ ቀበጥ ነኝ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹 💪
የባህር ዳሯ ቀበጥ ነኝ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹 💪
Open In TikTok:
Region: ET
Friday 04 September 2026 15:40:40 GMT
76860
2375
57
669

Music

Download

Comments

amoraw.g
Amoraw G :
ገና ፍርድ ቤት ያልቀረቡ ሰወችን ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ጥፋተኛ ሳይባሉ የተጠረጠሩ የተያዙ ሰወችን ወንጀለኛ ናቸው ብሎ ፎቶ ማሳየት ይቻላል እንዴ ?
2026-09-04 18:06:24
4
deju1e
deju :
በዘረፋት ብር ይወጣሉ የፌዴራል መንግስት ይየው
2026-09-04 23:08:36
8
deju1et1
Dejenie :
ድሮ የገበሬ ልጅ ፈራ እግዚአብሔር ያደረበት ነውርን እሚያውቅ ነበር አሁን ግን በተቃራኒው....
2026-09-04 21:23:05
7
adugnaeshetie
የማይረሰዉ ጌታ :
ተርጋግጦ እዉነት ከሆን አሰተማሪ ቅጣት እንጠብቃለን😳😳
2026-09-05 05:25:51
6
kimya487
kimya :
እገታዎች ላይ የመግስት የጰጵታ አባል ይኖሩበታል እጅ ማንም ዝዉ ብሎ ገብቶ ከተማ መሀል ሰዉ አግቶም ሆነ ገሎ አይሂድም
2026-09-05 07:05:32
4
user70420327807041
ቆፍጣናው :
እንዴው እገታን መጀመሪያ ያመጣው የትኛው አካባቢ ነው
2026-09-05 11:44:00
0
user25044413542765
user25044413542765 :
እኔ ግን እውነት አይመስለኝም
2026-09-04 19:26:22
1
addis.makbel
Addis Makbel :
መግሰት ይችላላል
2026-09-05 04:46:57
2
bedruadem307
በቡ :
ፖሊሱም?
2026-09-05 16:59:20
1
dibekulu62
ዲበኩሉdibekulu :
እረ ስማቸውን ጭምረ ላክው ለወደፊት እንጠንቀቅ
2026-09-05 03:44:00
1
user1190747349723
mesi :
ወይ ጉድ
2026-09-05 16:03:27
0
24ab86
24AB :
ገንዘብ ካለ ነገ ይፈታሉ
2026-09-04 18:22:47
2
ereki06
ereki :
ሰው ግን ምን እየሆነ ነው በዚ ልክ ዝቅ ማለት ይቻላል እንዴ ህሊና እሚባል ነገር ቀረ ወይኔ ጉድ😏😏
2026-09-05 18:06:10
0
.mekdi_27m
mekdi-27 :
ገና ምኑ ተነካ
2026-09-05 05:58:56
1
sade5613
abdu yssofe :
የራሳቸው የመንግስት አካላት ናቸው የሜያግቱ
2026-09-05 15:36:13
0
bartholo.sadetin
bartholo sadetin :
እኔንም chemrugn
2026-09-05 09:55:19
0
betselot8331
Anam :
እውነት ይወጣል
2026-09-05 08:27:41
0
user2435367161548
Miss_👭@ :
እናመሰግናለን በርቱልን
2026-09-05 11:14:51
0
belete.alemneh2
Belete Alemneh :
i ባህርዳር
2026-09-05 06:18:04
0
kutibar1
nunu :
አማ
2026-09-05 07:37:23
0
user74747711112
user747477102033 :
አልገባኝም ፖሊሶች አብረው አግተው ነው የተፖሰቱት
2026-09-06 00:36:46
0
melkamuamhara80e.c
Melkamu Amhara :
ፖሊሱም አጋች ነው እንዴ???
2026-09-05 06:30:33
0
mandabahirdar
man :
ተጠረጠሩ ማለት ወንጀለኛ ናቸው ማለት ነው
2026-09-04 22:31:56
2
awaju23
AWAJU KEFYALEW :
ለእገታ ስራ የዋለው የመግግስት ተሽከርካሪ የየትኛው ተቋም እንደሆነ ለምን ከመግለፅ ተቆጠባችሁ❓❓❓❓
2026-09-05 17:35:57
1
user3548169402067
user3548169402067 :
እንዲቀጥል አንፈልጋለን ሰው ተሰዶ አለቀ እገታውን በመፍራት
2026-09-05 17:27:33
2
To see more videos from user @mariedeem2y, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos


About