@salamkonjo2: #duetwith #ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ የተሰጠ መግለጫ፦ በአገራችን ኢትዮጵያ ከተሸነፉ የቅኝ ግዛት ወራሪ ኃይሎች ፍላጎት የተቀዳው ፀረ አማራነት ትርክት፣ ላለፉት 50 ዓመታት የአማራ ህዝብን በገዛ አገሩ ለአካላዊ፣ ለስነልቦናዊ፣ ለፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ለዘርፈ ብዙ ጉዳቶች አጋልጠውት ቆይተዋል። ይህ ፀረ አማራነት ትርክት በሂደት እያደገ መጥቶ በዋናነት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በነበረው አገዛዝ ሕጋዊ ቅቡልነት አግኝቷል። በሂደት ደግሞ ሕገ መንግስታዊ መዋቅራዊ ድጋፍ ተበጀቶለት፣ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ በተለያዩ ክፍሎች የአማራ ህዝብን ለዘር ጭፍጨፋና ለዘር ማፅዳት ዳርጎታል። ለሁለንተናዊ የህልውና አደጋም አጋልጦታል። በአማራ ህዝብ ጥላቻና የሀሰት ትርክት ተኮትኩቶ ያደገው የኦህዴድ ብልፅግና አለቃ አብይ አህመድ የአጤ ምኒልክ መንበርን በማደናገር ከያዘበት መጋቢት 24/ 2010 ዓ.ም ጀምሮ፣ የአማራ ህዝብ ሞት ከየ ሚዲያዎች ገፅ የማይጠፋ የየዕለት ዜና ሆኗል። ይህ የአማ፨ ህዝብ መዋቅራዊ የየዕለት ጭፍጨፋ መፍትሔ እንዲያገኝ ህዝባችን በበርካታ ሰላማዊ መንገዶች ጥያቄዎችን ለአገዛዙ ቢያቀርብም መልስ ሳያገኙ ቀርተዋል። ይባስ ብሎ፣ ይህ መንግስታዊ ድጋፍና እውቅና የተሰጠው የአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ ጥቃት ከመጋቢ /2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ጠቅላይ ግዛቶቹ እንዲገባ ተደርጓል። የኦህዴድ በግልፅግና አገዛዝ ከአሽከሩ ብአዴን ጋር በማበር የአስቸኳይ ጊዜ አዎጅ አውጥቶ በይፋ ህዝባችንን በሩ ድረስ በመምጣት መውረሩን ተከትሎ፣ የአማራ ህዝብ ራሱን ጨርሶ ከመጥፋት ለመታደግ ሲል ልጆቹን በፋኖነት አደራጅቶ ራሱን ከጥፋት መመከት ከጀመረ 3 ዓመታት ተሻግረዋል። ላለፉት ሶስት ዓመታት፣ አገዛዙ በአየርና በምድር አለኝ የሚለውን የኃይል አማራጭ ተጠቅሞ ህዝባችንን እየጨፈጨፈ ቢሆንም፣ ጀግናው ሰራዊታችን ፋኖ ህዝቡን አስተባብሮ እያደረገ ባለው ተጋድሎ የአገዛዙን ወራሪ ኃይል እንደየ አመጣጡ በመመከት ድልን መቀዳጀት ከጀመረ በርካታ ወራት ተቆጥረዋል። ስፊ ቀጠናዎችን ከአገዛዙ መዋቅር ውጭ በማድረግና በመቆጣጠር ሕዝባዊ መንግስት አቋቁሞ ህዝቡን ማስተዳደር ከጀመረ ዓመታት ተሻግረዋል። በዋናነት መሪ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ/ አፋብን/ በአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ጥረት ከተመሰረተ በኋላ የፋኖ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል በአገዛዙ ወራሪ ኃይል ላይ ከሚያሳርፈው የተቀናጀ ጥቃትና ከሚያገኘው ሁለንተናዊ ድል ባሻገር ከአገር አቀፍ አልፎ ዓለም አቀፋዊ እውቅናን እያገኘ መጥቷል። ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግላችን በዚህ ግለት እየሄደ ባለበት ወቅት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፣ ላለፉት ተከታታይ ቀናት ከአዲሱ ስራ አስፋፃሚ አባላት ጋር በአካል በመገናኘት ጥልቅ ውይይት አካሄዷል። ዕዛችን አዲሱን የስራ አስፈፃሚ አባለት አዋቅሮ ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወሳኝ ስራዎችን አከናውኗል። የተጓደሉ የኮር አመራሮችን ማሟላት፣ የየመምሪያውን የስራ ዕቅድ ማውጣትና መገምገም፣ በስልጠና የቆዩ ፋኖዎችን አስመርቆ ማሰማራትና አልፎ አልፎ ውጊያዎችን ማድረግ እንዲሁም ህዝባዊ መድረኮችን ማድረግና የሚዲያና ፕሮፖጋንዳ ስራዎችን ማከናዎን፤ ዕዛችን በአጭር ጊዜ ያካሄዳቸው የተለመዱ ተግባራት ናቸው። ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ በዚህ ወሳኝ ሂደት በመቀጠል ላለፉት ተከታታይ ቀናት ከአዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት፣ የየመምሪያ ዋናና ምክትል ኃላፊዎች፣ ከፋይናንስ ክፍሉና ከዕዛችን ሌሎች ተጨማሪ ወታደራዊ አደረጃጀቶች ጋር ሰፊና ጥልቅ ውይይት አካሄዷል። በዕዛችን ፖለቲካ መምሪያ በኩል ለውይይት መነሻ ይሆን ዘንድ የቀጠናውን የሶስት ዓመታት ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት አጭር ሰነድ ቀርቧል። ላለፉት ሶስት ዓመታት በጥልቀት ተፈትሸው ያልተከናወኑ ድርጅታዊ ተግባራትን በአጀንዳ በመለየትና በአካል በመወያየት ለቀጣይ ትግበራ የጋራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በቀጠናው የሚገኘውን ህዝባችንን ከምንጊዜው በላቀ ሁለንተናዊ ደህንነቱን በመጠበቅ ተገቢውን የህዝብ አስተዳደርና ማኀበራዊ አገልግሎት እንዲያገኝ በትጋት እንደሚሰራ፤ ጊዜያዊ የሕዝብ አስተዳደሩን ጨምሮ የዕዛችንን ከፍተኛ አመራሮች በተዋረድ እስከ ሻለቃ ድረስ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግሉን በማሳለጥ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡና የሚገኘውን የፋይናንስ ማዕከላዊነት፣ አሰባሰብና ቁጥጥር እንዲከታተሉ ማድረግ፤ ከዚህ ቀደም፣ በቀጠናችን በተበታተነ ሁኔታ ሲካሄድ የቆየውን የመማር ማስተማር ሂደት በተሳለጠና በባለቤትነት ስሜት እንዲካሄድ ፅኑ ፍላጎት እንዳለውና እንደሚሰራ፤ በዕዝ ደረጃ የተጓደሉ የትግል ኃላፊነት ቦታዎች እንዲሟሉና የሰራዊታችንንና የማኀበረሰባችንን ጥያቄዎችንና ቅራኔዎች በተደራጀ ሁኔታ በመመለስና በመፍታት፣ ድርጅታችንን ከምንጊዜውም በላይ በመጠበቅ፣ ድርጅታዊ ዓላማችንን ከግብ ለማድረስ በከፍተኛ ፅናትና ትጋት ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ እንደምንሰራ በውይይታችን አረጋግጠናል። እነዚህ የትግል ስራዎቻችንን በተሳለጠና በተጠና መልኩ ለማስኬድ ያስችል ዘንድ ስልታዊ ዓመታዊ እቅድ በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ፅ/ቤት በኩል ተዘጋጅቶ ለውይይት ቅርቧል። ስራ አስፈፃሚ አባላት ዕቅዱን በጥልቀት በመፈተሽና በማሻሻል በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል። የአፋብን፤ ቴዎድሮስ ዕዝ ስራ አስፋፃሚ አባላት፣ በአካል በመገናኘት ለተከታታይ 10 ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ በጥልቀት ያካሄደውን ድርጅታዊ ውይይት አስመልክቶ የሚከተሉት ነጥቦች በአስፈፃሚው በትኩረት እንዲሰራባቸው አቅጣጫ አስቀምጧል። 1ኛ, አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ በከፈተው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ምክንያት ትምህርት ቤቶቻችንን ለወታደራዊ ካምፕ አገልግሎት ሲጠቀማቸው ቆይቷል። የአገዛዙ ወታደሮች የትምህርት ተቋማት መቀመጫ ወንበሮቻቸውን ጨምሮ ሌሎች ቁሳቁሶችን በመሰባበር ለምሽግነትና ለማገዶነት አገልግሎት አውሏቸዋል። እያዋላቸውም ይገኛል። ከእነዚህ እኩይ ተግባራቱ በተጨማሪ በከባድ መሳሪያዎችና በድሮን ተቋማቱን በተከታታይ በመደብደቡና በማውደሙ ምክንያት ላለፉት 3 ዓመታት የመማር ማስተማር ስራው እንዲቋረጥ ለማድረግ ሞክሯል። ይሁን እንጂ፣ ዕዛችን በዚህ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተለይተው የቆዩ ተማሪዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ባልተሟላ ሁኔታም ቢሆን ከፊደል ገበታ ተለይተው እንዳይቆዩ ጥረት አደርጓል። ዛሬ ደግሞ ይህ የቆዬ ጥረታችን በተሟላና በተቀናጀ ሁኔታ መስከረም ወር 2019 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቀጥልና የትምህርት ማኀበረሰቡ፣ ሰራዊታችን፣ ህዝባችንና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ከምንጊዜው በላቀ ሁኔታ ርብርብ በማድረግ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አስፋፃሚ በወሰነው መሰረት እንዲተገበር እንሰራለን። 2ኛ, መሪ ድርጅታችን አፋብን ያወረዳቸውንና የሚያወርዳቸውን ድርጅታዊ የአሰራር መርሆች መመሪያዎች፣ ሕግና ደንቦችን ተቀብለን የምናስፈፅምና የምንፈፅም መሆኑንን አየገለፅን፣ ዕዛችን ከዚህ ቀደም የነበሩ ደካማ አሰራሮችን በጥልቀት ገምግሞ በመለየትና ስልታዊ ዓመታዊ ዕቅድ በማውጣት ለድርጅታችን፣ ለህዝባችንና ለሰራዊታችን ከምንጊዜው በላቀ ሁኔታ ዕቅዶቻችንን በጊዜ ለክተን በመስራት የሚታይ ውጤት ለማምጣት ቁርጠኛ አቋም መያዛችንን እናሳውቃለን። 3ኛ, በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ከዚህ ቀደም ይታዩ የነበ
ናዱ 2
Region: BH
Friday 04 September 2026 20:30:13 GMT
Music
Download
Comments
☑️☑️☑️ :
ድል ለጀግኖቻችን ✊🏽✊🏽አንድነታችሁ ይጠንክርልን🙏🙏🙏🙏
2026-09-04 22:20:06
0
ግዮናዊት 12🖤 :
ሲያምሩ🔥
2026-09-04 20:41:41
1
የዘሜ ዋMekdes ❤️ :
🥰🥰
2026-09-04 22:29:00
1
ልቤ💗ፍትሕ ለክርሥትያን ታደለ🥺( ገብርዬ) :
❤️❤️
2026-09-05 05:06:25
1
. :
❤️❤️💪
2026-09-04 22:39:50
1
genet :
🥰🥰🥰
2026-09-04 22:29:06
1
MULIY ዘ ሀበሻዊት B ❤Ⓜ🔐 :
❤❤❤🙏🙏🙏💪💪💪💪
2026-09-04 21:08:07
1
💙💙💙🤷♀️🤷♀️ :
💪💪💪
2026-09-05 06:04:12
1
ግሩሜ➛የአርበኛ ዛምራ ወንድም✍️ :
🥰🥰🥰
2026-09-04 20:33:25
1
Sara Adamu :
🥰🥰🥰
2026-09-05 07:07:26
0
To see more videos from user @salamkonjo2, please go to the Tikwm
homepage.