@afromekina: የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ከጀሞ ፒያሳ የፈጣን አውቶቡስ  መስመር ግንባታን በልዩ ትኩረት እየከናወነ እንደሚገኝ ገለጸ የአአዲስአበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳኛቸዉ ሽፈራዉ ከጣቢያችን ኢትዮ ኤፍ ኤም  ጋር በነበራቸው ቆይታ ከፍተኛ የትራንስፖርት ፍላጎትና የአቅርቦት አለመመጣጠን ለመፍታት የከተማ አስተዳደሩ የጀሞ-ፒያሳ የፈጣን አውቶቡስ  መስመር ግንባታን በልዩ ትኩረት እየከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ይህ 15 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ፕሮጀክት አውቶቡሶች ብቻ የሚጓዙበት የተለየ መስመር የሚኖረው ይሆናል ብለዋል። ወደ አገልግሎት ሲገባ በአንድ ጊዜ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ህዝብ የማጓጓዝ አቅም ስለሚኖረው፣ በአካባቢው የሚታየውን የታክሲ ሰልፍ በእጅጉ እንደሚያቃልል ይጠበቃል። የትራንስፖርት ቢሮው እንደገለጸው፣ ፕሮጀክቱ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የክትትል ስርዓት የሚኖረው ሲሆን፣ አውቶቡሶቹ የሚመጡበትን ሰዓት ተሳፋሪዎች አስቀድመው እንዲያውቁ የሚያስችል አሰራርም ይኖረዋል ብለዋል። ይህ የትራንስፖርት ስርዓት በሌሎች የከተማዋ ዋና ዋና መስመሮች ላይም ተሞክሮው እንዲሰፋ እቅድ ተይዞለታል ተብሏል። #afromekina

🅐🅕🅡🅞𝖬𝖤𝖪𝖨𝖭𝖠
🅐🅕🅡🅞𝖬𝖤𝖪𝖨𝖭𝖠
Open In TikTok:
Region: ET
Tuesday 08 September 2026 05:47:34 GMT
14296
71
1
2

Music

Download

Comments

demlie.bitew
Demlie Bitew :
staircase family planing mother land lada ride and promise land Dane techn craft manpower condominiums busses
2026-09-08 09:12:20
0
To see more videos from user @afromekina, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos


About