@juless.nd: #carreras #carrevip #fyp #viraltiktok

Jules
Jules
Open In TikTok:
Region: SN
Monday 14 September 2026 10:21:50 GMT
212
18
0
2

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @juless.nd, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

‹‹መስከረም 4›› በዚች ዕለት የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ የልደቱ መታሰቢያ በዓሉ ነው። ሐዋርያው ዮሐንስ ከዘብድዮስና ከማርያም ባውፍልያ መስከረም አራት ቀን ተወልደ ። ዮሐንስ ማለት ትርጓሜው
‹‹መስከረም 4›› በዚች ዕለት የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ የልደቱ መታሰቢያ በዓሉ ነው። ሐዋርያው ዮሐንስ ከዘብድዮስና ከማርያም ባውፍልያ መስከረም አራት ቀን ተወልደ ። ዮሐንስ ማለት ትርጓሜው "እግዚአብሔር ፀጋ ነው፣ ደስታ" ማለት ነው። ቅዱስ ዮሐንስ የጌታችን ደቀመዝሙር ከመሆኑ አስቀድሞ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ነበር ገና በወጣትነቱም የመሲሁን የክርስቶስን መምጣት ከመምህሩ ከመጥምቀ መለኮት ስለተረዳ የጌታችን ደቀ መዝሙር ሆኗል፤ ዕድገቱም በገሊላ ነበር። ለጌታ ቅርብ ከነበሩ የምስጢር ሐዋርያት ( ጴጥሮስና ያዕቆብ) ቀዳሚው እርሱ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ ልክ ወንጌሉን ሲጀምር " በመጀመሪያ ቃል ነበረ፥ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ ይላል። በኑሮም ጌታ ስለሚመስል (ፍቁረ እግዚእ) ይባለል። ነገረ መለኮትን በበለጠ ከሌሎች አምልቶ አስቶ በጥልቀት በማስተማሩ ነባቤ መለኮት (ታዖሎጎስ)ተሰኝቷል። ስለጌታም ባለው ቅናት ባሳየው የሀይል ሥራ በኦኔርጌስ (ወልደ ነጎድጓድም) ተብሏል። ፍጥሞ በምትባል ደሴት በራዕይ መጻእያትን በመግለጡ ባለራዕይ (በግሪክ አቡቀለምሲስ) ይባላል። በዕለተ ዓርብ በመስቀል ሥር ተገኝቶ የጌታን መከራ መስቀል በማየቱ ፊቱ በሀዘን ስለተቋጠረ ቁጽረ ገጽ (ፊቱ በሀዘነ የተቋጠረ) ስምም ተሰቶታል። ጌታችን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ ከአጠገቡ ያልተለየ፣ ስቃይና መከራውን ያየ፤ በዚህም የተነሳ ለ፸ ዓመታት ፊቱ በሀዘን የተቋጥረ (ቁጽረ ገጽ) ሐዋርያ ነው። ከሐዋርያት መካከል ሞትን ያልቀመሰ እንደ ሔኖክ፣ ኤልያስ በብሔረ ሕያዋን የሚኖር ሐዋርያ ነው። የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በረከትና ምልጃ አይለየን! #viralreelschallenge

About