@iwannasleepforever.hmm:

SULIYYZA.
SULIYYZA.
Open In TikTok:
Region: KH
Thursday 16 July 2026 13:38:19 GMT
20
10
0
1

Music

Download

Comments

There are no more comments for this video.
To see more videos from user @iwannasleepforever.hmm, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos


"#መጽሐፍ_ቅዱስ_ብቻ የሚለው ትምሕርት ፈጽሞ ከክርስትና የተለየ አስተሳሰብ ነው። ምክኒያቱም የጌታ ፍቃድ ገና ከጅምሩ በመንፈሱ በኩል ከእርሱ ጋር አንድ ሆነን እንድንኖር እንጂ በመጽሐፍ በኩል እንድንኖር አልነበረምና። ቤተ ክርስቲያን ያለ መጽሐፍ ቅዱስ የኖረችበት ጊዜ አለ፤ የሃዲስ ኪዳን መጻሕፍት የተጻፉት ቤተ ክርስቲያን ተመስርታ ብዙ ክርስቲያኖች በክርስቶስ ካመኑ በኋላ ነው በራሷ በቤተ ክርስቲያን የተጻፉት። በተለይም ድንቅ የሆነው የዮሐንስ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን ከተመሰረተች ሰባ አመታት በኋላ የተጻፈ ነው። ታድያ ግን ምንም እንኳን ያለ መጽሐፍ ቅዱስ መኖር ብትችልም ያለ መንፈስ ቅዱስ ግን ኖራ አታውቅም ልትኖርም አትችልም ምክኒያቱም ክርስቶስ ከቤተ ክርስቲያን ጋር አንድ ሆኖ የሚኖረው በመንፈሱ በኩል ነውና። ለዛም ነው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ በማለት የሚናገረው፡ “እግዚአብሔር ሕዝቡን ማግኘት የሚፈልገው በመጽሐፍ ሳይሆን ቀጥታ በራሱ ነው.. እነ ኖኅን እነ አብረሃምን እንዲሁም ልጆአቸውን እንዳገኛቸው.. በኋላም ራሱን ሙሴንም በራሱ እንዳናገረው.. ከዛ በኋላ ግን ሕዝቡ ከእነርሱ የማይጠበቅ ኃጢዓትን ሲያደርጉ ግንኙነቱ በጽሑፍ ደግሞ ሆነ። ይህ ነገር ለሃዋርያትም ጭምር ነው.. ጌታ ወደ እውነት ሁሉ እንዲመራቸው ለሃዋርያቱ የሰጠው መጽሐፍን ሳይሆን ቅዱስ መንፈሱን ነው። በኋላ ግን ከዶግማ እና ከሕይወትም ጋር ተያይዞ ለማስታወሻነትም በጽሑፍ ሰፈረ።” በማለት ይናገራል። ከዚህም ደግሞ ክርስቶስ ለሐዋርያት የሰጠው መጽሐፍ ሳይሆን መንፈሱን እንደሆነ ልብ ልንለው ይገባል። መጽሐፉ የተጻፈው በፈሰሰላት መንፈስ በመነሳሳት በቤተ ክርስቲያን ነው።" (#ትውፊትና_መጽሐፍ_ቅዱስ ወንድም አክሊል) ስለ ትውፊት ጌታ ቢፈቅድ በቪዲዮ እከሰት ይሆናል @ኢዮብ-ዘ-ሚካኤል @ሐዋርያዊ መልሶች - Apostolic Answers @Dn Wonde ye12 @lemu

About