@mr.alog4:

Mr Alog
Mr Alog
Open In TikTok:
Region: GH
Wednesday 12 August 2026 09:30:47 GMT
17547
1108
25
106

Music

Download

Comments

saviour28305
Ajeh furniture :
Praying for massive work like this
2026-08-19 20:05:09
0
ta.classical.furn
T&A CLASSIC :
if nah 207 furniture do this one na everybody for tik tok no go here word again 😅😹😹
2026-08-18 22:29:17
1
ecolet5
Ecolet :
Na so
2026-08-19 14:28:44
0
ayobamihamza
A Y O B A M I D E L E🪖 :
Let me calm down learn this furniture thing well oo..cos na everyday person Dey see new features
2026-08-17 16:38:25
1
gramtainment
GRAMTAINMENT :
This is futuristic
2026-08-12 20:42:21
3
profarmer_marshall
Marshall The Farmer :
how much
2026-08-12 23:10:14
0
nolimitfarms
No Limit’s Farms 🐏 🐐🇬🇭 :
You Dey Ghana
2026-08-16 17:41:46
0
josephsackey788
king legacy :
Poverty is a bastard 💯💯😳
2026-08-13 06:15:42
0
flexhomeinterior
Abiodun City :
Impressive 💯
2026-08-17 18:36:45
0
alebinosman
𝑶𝑺𝑴𝑨𝑵𝑺𝑭𝑼𝑹𝑵𝑰𝑻𝑼𝑹𝑬 :
Oops 🙊
2026-08-12 23:56:28
0
man_kante1
K A N T E :
2026-08-12 22:51:12
1
bandexinterior
Bandex Home Decor🇳🇬🇬🇭 :
Nice work
2026-08-15 09:39:51
0
mawuena633
mawuenamawuena617 :
Fantastic 👍
2026-08-14 21:39:50
0
success.exotics
Success Exotics :
ku333🥰
2026-08-12 22:41:12
0
saviour28305
Ajeh furniture :
Good job
2026-08-19 20:05:17
0
pess.construction
PESS CONSTRUCTION&ELECTRICALS :
2026-08-13 16:23:11
0
roddyricch868
RoddyRicch686 :
✌✌✌
2026-08-12 19:23:21
1
z.furniture1
z.furniture1 :
💯😊
2026-08-12 18:11:29
1
lonelybird69
lonely bird 🪽 :
🙏🙏🙏
2026-08-15 12:35:49
0
brandesfurniture
brandesfurniture :
💯
2026-08-13 09:16:48
0
appiah.dennis91
Appiah Dennis :
✌✌✌
2026-08-12 22:42:36
0
francis.anderson05
Francis Anderson :
🥰🥰🥰
2026-08-12 20:53:57
0
tianabby44
🌼Tiana🦋 :
🥰🥰🥰
2026-08-14 21:21:32
0
To see more videos from user @mr.alog4, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos


"መለስ" ሆይ እስቲ ጉዳችንን ስማን ልንገርህ እኛን አትጠይቀኝ በቁም ሞተናል እስቲ ትንሽ ላጫውትህ ግን አደራ እንዳትጨነቅ አሁን ከዚህ በታች የምትሰማው ሁሉ ኑሯችን ነው እንዳትደነግጥ! .**** አንተ ከሄድክበት ዓለም ሆኖ የልጆችን የልብ ምት መስማት ቢቻል ኖሮ፣ ይሄኔ የዚህች ምድር ጩኸትና የጦቢያ የልጆቿ የደከመ ትንፋሽ እረፍት ይነሳህ ነበር። እነሆ ዛሬ አንተ ከዚህች ምድር ከተለየኸን ሙሉ ዐሥራ አራት ዓመታት ተቆጠሩ። .**** ጊዜው እንዴት ይሮጣል? ግን ለአንተ ዓመታቱ ቢሮጡም፣ ለእኛ ግን እያንዳንዱ ቀን እንደ ሺህ ዓመት የከበደ፣ በፈተና እና በብቸኝነት የተሞላ ረጅም ጉዞ ነበር። ልክ አባቱን በድንገት ሳያስብ እንደተነጠቀና ሜዳ ላይ እንደቀረ ምስኪን ልጅ የገባንበትን አውሎ ንፋስና የገጠመንን የሕይወት ውጣ ውረድ ብታየው፣ ልብህ በሐዘን ይሰበር ነበር። እንኳንም አያለህን! .**** አባታችን መለስ ሆይ አንተ እኮ ለእኛ መሪ ብቻ አልነበርክም፤ የሀገሪቱ የቤቱ ዋልታ፣ የአዕምሮው ማዕበል፣ በማዕበል የተናወጠችውን መርከብ ወደ ወደብ የምታሻግር ብልህ መሪ ነበርክ። ደግሞም አሻግረሀን ብዙ አሳይተህን ነበር እኔም ሌላውም ስራህም ህያው ምስክር ነን! .**** ዓለም ያደነቀው አንደበተ ርቱዕነትህ፣ በዓለም መድረኮች ላይ እንደ ሻማ የምታበራው ጥልቅ ዕውቀትህ፣ ማንኛውንም ውስብስብ ችግር በአንድ ፅንሰ ሐሳብ ፈትተህ የምታስቀምጥበት ያ ድንቅ ብቃትህ ዛሬ እንዴት እንደናፈቀን ብታውቅ! ምኞቴ ነበር። .***** በዓለም ዙሪያ ያሉ ኃያላን አንተ ስትናገር ጆሮ ሰጥተው በመፍዘዝ የሚያዳምጡበት፣ የአፍሪካን ክብር በጫንቃህ ተሸክመህ ድምፅ የሌላቸውን ድምፅ የሆንክበት ያ ታላቅ ግርማ ሞገስህ የት ደረሰ? ብዪ ለመጠየቅ አስብ እና ለካስ እረፍት ላይ ነህ ብዪ ሳስብ ላለማስጨነቅ ዝም እላለሁ። .**** መለስ ሆይ አንተ ትተኸን ከሄድክ በኋላ… .**** እየውልህ አባቴ፤ አንተ ከሄድክ በኋላ እኛ ስንት ጦርነት፣ ስንት ስቃይ፣ ስንት በደል አሳለፍን መሰለህ? አንተ የገነባኸው የአንድነት ድልድይ ሲናድ፣ ወንድም በወንድሙ ላይ ሲነሳ፣ እናቶች የልጆቻቸውን አስከሬን ማቀፍ የዕለት ተዕለት ኑሯቸው ሲሆን በአይናችን አየን። .**** ትናንት በልማትና በዕድገት እናሸንፋለን ያልከን ድህነት ዛሬ መልኩን ቀይሮ መጣ፤ የሰው ልጅ ሕይወት እንደ ቅጠል ረገፈ። ወጣቶች ልክ እንደ ደርግ ዘመን በፍርሀት ድባብ ተከበዋል ዛሬ አንድ ወጣት ከኑሮ ውድነቱ ባሻገር እታፈስ ይሆን? የሚለው ስጋት እረፍት ነስቶታል! .**** የወጣቱ ተስፋ አልባነት ያስፈራል ያ ለነገው ተስፋ ታጭቶ የነበረው ወጣት ዛሬ ፊቱ በባዶነት ተሞልቷል። ሥራ አጥነቱ፣ የነገው ፍርሃትና የህልም አልባነቱ ገደል ውስጥ ከቶታል፤ ሀገሩን ጥሎ በየበረሃውና በየባሕሩ ለመሰደድ ይማስናል። .***** የኑሮው አላነሳብህም! ብዪ ነበር ግን አልቻልኩም! ዛሬ በየቤቱ ያለው የኑሮ ውድነት ቃላት አይገልጹትም። አንድ አባት ለልጆቹ የዕለት እንጀራ ማቅረብ አቅቶት አንገቱን ደፍቶ ሲያለቅስ ማየት የተለመደ ሆኗል። የድሃው ዕሮሮ ጣሪያ ሰማይ ነክቷል፤ የሕዝቡ ትዕግሥት ተሟጧል። .***** ዛሬ ህዝቡ በቤት ኪራይ ተማሯል አንዳንዱ ልጆቹን በትኖ ጎዳና ወጥቷል። አንዳንዶች የማያውቁት ሰፈር ሄደው ለምነው ሲመሽ ወደ ሰፈራቸው ይመለሳሉ። እንዲህ የምልህ ስራ ያላቸው የመንግስት መስሪያቤት የሚሰሩ ናቸው ከስራ በኋላ የማያውቁት ሰፈር ሄደው የሚለምኑት። .***** ይቺን ልጨምርልህ ደግሞ የማኅበራዊና ሃይማኖታዊ እሴቶቻችን ተደረማምሰዋል ቅጥ አጥተዋል ፡ አንተ አጥብቀህ የምትጠብቀው የሕዝቦች መከባበር፣ ያ የዘመናት አብሮነት እና የሃይማኖቶች መቻቻል ፈተና ላይ ወድቋል። በደምና በአጥንት የተገነባው ማኅበራዊ ማሰሪያችን ሲላላ፣ “አባት አልባ ሆንን” እያልን በየማዕዘኑ ህዝቡ ያነባል። .***** ስለ ፊንፊኔ ትንሽ ልንገርህ እና ልጨርስ ዛሬ አዲስ አበባን ብታያት በመንገዶቿና በሕንፃዎቿ ብልጭልጭ ነገሮች ተሞልታለች። የማነች የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ ማለት ነው። መብራቶቹ ይበራሉ፣ አዳዲስ አስፋልቶች ተነጥፈዋል፤ ግን ያ አንተ ትፈራው የነበረው እውነት ዛሬ ገሃድ ሆኖ ቁጭ ብሏል።“ውበቱና ብልጭልጩ ቢበዛም፣ ሰው በገዛ ሀገሩና በመንደሩ ባይተዋር ሆኗል!” .**** የአዲስ አበባ ሕዝብ በዚያ ብልጭልጭ ገፅታ ውስጥ ሆኖ ውስጡ ግን በስቃይና በዋይታ ይቃጠላል። የፈረሰው ቤቱ፣ የተነጠቀው ትውስታው፣ በአካባቢው ላይ ያለው የባለቤትነት ስሜት መጥፋት ልቡን አድምቶታል። .***** ውጫዊው ግርማ ሞገስ የውስጡን የደስታ ማጣት ሊደብቀው አልቻለም። ሰው በገዛ ሀገሩ እንደ እንግዳ፣ በገዛ አፈሩ ላይ እንደ ባይተዋር ሆኖ አንገቱን ደፍቶ ይራመዳል፤ ፈገግታው የይስሙላ፣ ውስጡ ግን በለቅሶ የታጨቀ ነው። .**** መለስ ሆይ ዛሬ እኮ እውነተኛ መካሪ፣ በማዕበል መሀል ኮምፓስ ሆኖ አቅጣጫ የሚያሳይ አርቆ አሳቢ መሪ አጥተናል። ያ የአንተ የተረጋጋ፣ ጥልቅና አሳማኝ አመክንዮ ዛሬ በፉከራና በውዥንብር በግርግር ተተክቷል። ልክ ድንገት ጨለማ ውስጥ የቀረ ልጅ “አባቴ የት ነህ?” ብሎ እንደሚጣራ ሁሉ፣ ዛሬም ይህች ሀገርና ልጆቿ ያንተን ጥልቅ ዕውቀት፣ ያንተን ቆራጥነት እና የዳበረ የመሪነት ስብዕናህን በብርቱ ይናፍቃሉ። .***** ዐሥራ አራት ዓመታት አለፉ በዚህ ጊዜም በአንተ መሞት የሚደሰቱ ጮቤ የሚገርጡ መኖራቸውን ሳልነግርህ አላልፍም ነገር ግን እኛ ወዳጆችህ አሁን ድረስ በልባችን የፈጠርከው ክፍተት አልተሞላም፤ ያንተ ባዶነት ዛሬም እንደ ትኩስ ቁስል ያማል። .**** ነፍስህ በሰላም ትረፍ አባታችን፤ ስምህና ያ ድንቅ አሻራህ በታሪክ ማኅደር ውስጥ ለዘላለም ሲነበብ ይኖራል! #ትግራይ_ንዘለኣለም_ትነብር🙏🇻🇳 #ethiopian_tik_tok🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹 #eirtrean_tiktok🇪🇷🇪🇷🇪🇷eirtrean #አማራዬ💚💛❤አማራዬ💚💛❤ #oromotiktok

About