@bnt.2o:

bnt.2o
bnt.2o
Open In TikTok:
Region: SA
Sunday 20 September 2026 07:38:29 GMT
258
4
1
1

Music

Download

Comments

user9575925830986
ملكة :
🥰🥰🥰
2026-09-20 09:53:27
0
To see more videos from user @bnt.2o, please go to the Tikwm homepage.

Other Videos

#ሐሙስ_መንኩሳ_ቅዳሜ_አረፈች  ​አንዲት ወጣት ልጅ በጣም ትታመማለች፤ ከህመሟ ለመዳንም ወደ ገዳም ትሄዳለች። ገዳም ገብታ ህመሟን ተቆቁማ መነኮሳትንና ነዳያንን በጉልበቷ ታግዝ ነበር። ገዳም በገባች በሁለተኛ ዓመቷ ከህመሟ ትድናለች። እናም ከጓደኛዋ ጋር ሆና ዋሻ ከዘጉት አባት ዘንድ ይሄዳሉ። ​የዚያን ጊዜም አባ
#ሐሙስ_መንኩሳ_ቅዳሜ_አረፈች ​አንዲት ወጣት ልጅ በጣም ትታመማለች፤ ከህመሟ ለመዳንም ወደ ገዳም ትሄዳለች። ገዳም ገብታ ህመሟን ተቆቁማ መነኮሳትንና ነዳያንን በጉልበቷ ታግዝ ነበር። ገዳም በገባች በሁለተኛ ዓመቷ ከህመሟ ትድናለች። እናም ከጓደኛዋ ጋር ሆና ዋሻ ከዘጉት አባት ዘንድ ይሄዳሉ። ​የዚያን ጊዜም አባ "ልጄ አንቺ መመንኩስ አለብሽ፤ ጓደኛዋን ደግሞ አንቺ ወደ ዓለም ተመለሽ፣ አግብተሽ ወልደሽ ፈጣሪን አገልግይ" ሲሉ… እሷ ማልቀስ ትጀምራለች። ​ለቅሶዋም "እኔ ሳልበቃ መመንኮስ አልፈልግም ነበር" የሚል ነበር። አባንም "እባክዎ ባይሆን ሰውነቴ እስኪደክም በጉልበቴ ላገልግል" ትላቸዋለች። አባ ብዙ ሊያሳምኗት ቢሞክሩም እንቢ ስትል፣ በመጨረሻም "አይሆንም፤ እመቤርሃን ተደጋጋሚ እንድትመነኩሽ መልእክቱን እንዳደርስሽ ነግራኝ ነው" በማለት በአባታዊ ተግሳጽ ያዝዟታል። ​እሷም ምርር ብላ እያለቀሰች፦ "እመቤርሃን እናቴ፣ የእኔ ጸሎት ይሄ ነበር? ምንኩስና ፈተና ነው። እኔ ደግሞ ፈተናውን መወጣት አልችልም። እባክሽ የማልወጣውን ፈተና አትስጭኝ። እባክሽ ልጅሽን ለምኝልኝ፤ በፈተና መውደቅ አልፈልግም። መመንኩስ አልፈልግም! ምንኩስናን ጠልቼው ሳይሆን ምንኩስና ስለማይገባኝ ነው" እያለች ከልቧ ታነባለች። ​ጊዜው ደርሶ "ከሰነፍ መስዋዕት መታዘዝ ይበልጣል" ነውና ለግላጋዋ ወጣት አምናበት ሐሙስ ትመነኩሳለች። ​ልመናን የማትረሳ ወላዲት አምላክም በፈተና እንዳትወድቅባት ወደ እሷ ያመጣት ዘንድ ልጇን ማልዳ ሐሙስ መንኩሳ በሦስተኛው ቀን ቅዳሜ ለታ መለስ አሸለበች፤ ከዚህ ዓለም ድካም አረፈች። ​ታሪኩ የተፈጸመው በ2016 ዓ.ም ነው፤ እኔ ደግሞ በ2017 ዓ.ም በዲማ ጊዮርጊስ ገዳም ጓደኛዋ የነገረችኝን ምስክርነት ሳልጨምር ሳልቀንስ እውነተኛ ታሪኳን አወራኋችሁ። ከታች ያለው ፎቶ ምሳሌ እንጂ ትክክለኛ የእሷ ፎቶ አይደለም። ​በሕይወቴ እንዲህ አይነት ቅናት ቀንቼ አላውቅም፤ የምር ብዙ ነገር የተማርሁበት ታሪክ ነው። ጓደኛዋ ስለልጅቷ ስትናገር "ደግ፣ ሩህሩህ የሚል አይገልጣትም፤ ሲበዛ በጣም ዝምተኛ ነበረች" ትላለች። ቀንም ማታም ብትሰራ አታክትም ነበር፤ በእሷ ልክ የበረከት ስራ የሚሰራ የለም። እጅግ ሲበዛ የክርስቶስ ፍቅር ነበረባት። ህመሟን ጉዳይ አትለውም፤ እረፍት የሚባል ነገር አይታይባትም ነበር። ቀን በሥራ፣ ማታ በጸሎት ትተጋ ነበር። ​"እኔ ይሄው ከቤቴ ከወጣሁ 7 ዓመት በየገዳሙ እዞራለሁ፤ ያተረፍሁት ነገር ግን የለም። እህቴ ሁሌም በአይኔ ትመጣለች" ነበር ያለችው። ​የምር በዚህ ዘመንም እኮ በየገዳሙ ትንግርት የሆኑ ሰዎች አሉ። መታደል እኮ ነው! እኛንም ለእንደዚህ አይነት የክብር ሞት ያብቃን።

About